የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በቁጥር 30/2018 በ2018 በጀት ዓመት አህጉራዊና አለም አቀፍ ውድድሮችን ስለሚያደረግ አትሌቶችን ሆቴል አስገብቶ ስልጠና ስለሚሰጥ ከባለ 3 እና ከባለ 4 ኮከብ ሆቴል አገልግሎት ለማግኘት በሀገር ውስጥ ግልጽ ጨረታ ማወዳደር ይፈልጋል።
የሆቴል ግልፅ የጨረታ ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በቁጥር 30/2018 በ2018 በጀት ዓመት አህጉራዊና አለም አቀፍ ውድድሮችን ስለሚያደረግ አትሌቶችን ሆቴል አስገብቶ ስልጠና ስለሚሰጥ ከባለ 3 እና ከባለ 4 ኮከብ ሆቴል አገልግሎት ለማግኘት በሀገር ውስጥ ግልጽ ጨረታ ማወዳደር ይፈልጋል።
በዚሁ መሠረት፡-
1. በጨረታው ለመወዳደር የምትፈልጉ ተጫራቾች የታደሰ ንግድ ፍቃድ ያላቸው፣ የኮከብ ደረጃ ሰርተፊኬት ማቅረብ የሚችሉ፤ የቲን እና ቫት ተመዝጋቢ የሆኑ።
2. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ ብር 10,000.00 (አስር ሺህ ብር) ከጨረታ ሰነድ ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው።
3. ተጫራቾች ጨረታውን በሪፖርተር ጋዜጣ ከወጣበት ዕለት አንስቶ ለተከታታይ 10 የስራ ቀናት የማይመለስ ብር 1000.00 (አንድ ሺህ ብር) በመክፈል ጉርድ ሾላ በሚገኘው በፌዴሬሽኑ 2 ፎቅ ቢሮ ቁጥር 6 በመምጣት የጨረታ ሰነዱን መግዛት ይችላሉ።
4. ተጫራቾች የመጫረቻ ሰነዶቻቸውን ዋናውንና ኮፒውን በታሸገ ኤንቨሎፕ ማስታወቂያ ከወጣበት ዕለት ጀምሮ ለተከታታይ 10 የሥራ ቀናት በፌዴሬሽኑ ቢሮ ቁጥር 5 ለጨረታ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል።
5. ጨረታው ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በአስረኛው ቀን በ4፡00 ሰዓት ታሽጎ በዚያው ዕለት 4፡30 ሰዓት በፌዴሬሽኑ ቢሮ ቁጥር5 (መሰብሰቢያ አዳራሽ) ይከፈታል።
6. ተጫራቾች የሚወዳደሩባቸውን አገልግሎት ቫትና ሰርቪስ ቻርጅን ጨምሮ ያለውን ዋጋ ማስቀመጥ ይጠበቅባቸዋል።
7. ፌዴሬሽኑ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
አድራሻ፡- ጉርድ ሾላ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ሕንፃ 2ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 6
ለበለጠ መረጃ:- 0116-47-97-94/ 0116-47-95-78 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ።
ፋክስ 0116-45-08-79
ፖ.ሳ.ቁ 13336
የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን
