የድርጅታችን ኮሜርሻል ኖሚኒስ ኃ/የተ/የግል ማህበር ለቂርቆስ ቅርንጫፍ የፓርቲሽን ስራ ተጫራቾችን አወዳድሮ ስራ ማሰራት ተፈልጓል፡፡
የጨረታ ማስታወቂያ CN/NCB/24/18
የድርጅታችን ኮሜርሻል ኖሚኒስ ኃ/የተ/የግል ማህበር ለቂርቆስ ቅርንጫፍ የፓርቲሽን ስራ ተጫራቾችን አወዳድሮ ስራ ማሰራት ተፈልጓል፡፡
በዚህም የህንጻ ፓርቲሽን ስራ መስራት የሚችሉ ድርጅቶችን በሀገር ዓቀፍ ግልጽ ጨረታ ደረጃ 6 የህንጻ ተቋራጮችን አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል፡፡ በመሆኑም ተጫራቾች የታደሰ የንግድ ፈቃድ፣ በጨረታ ላይ መሳተፍ እንደሚችሉ የሚገልጽ ደብዳቤ፣ በአቅራቢዎች ዝርዝር ውስጥ የተመዘገቡትን ማስረጃ፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ፣ የምዝገባ ሰርተፍኬት የመሳሰሉትን የቴክኒከ ሰነዶች በተለየ የታሸገ ፖስታ እንዲሁም ፋይናንሻል ዶክመንት በተለየ ሁለተኛ የታሸገ ፖስታ በማድረግ እንድትወዳደሩ ይጋብዛል፡፡
የጨረታ ዶክመንቱን ቦሌ መንገድ ደንበል የገበያ ማዕከል ጀርባ በሚገኘው የድርጅቱ ዋና መ/ቤት ህንፃ 5ኛ ፎቅ የግዥ ዋና ክፍል ብር 100 በመክፈል ከሰኞ እስከ ዓርብ (ጠዋት 2፡00-6፡00 እንዲሁም ከሠዓት 7፡00- 11፡00 እና ቅዳሜ ግማሽ ቀን ጠዋት ማግኘት ይቻላል። የጨረታ ማስከበሪያ የህንጻ ፓርቲሽን ስራ ብር 25,000 (ሃያ አምስት ሺህ ብር) በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ከመጫረቻ ዶክመንት ጋር መቅረብ ይኖርበታል፡፡ ተጫራቾች የመጫረቻ ዶክመንታቸውን ከላይ በተቀሰው አድራሻና የሥራ ሰዓት በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ እስከ ሚያዚያ 6 ቀን 2018 ዓ.ም 4፡00 ጠዋት ድረስ ማስገባት ይችላሉ፡፡ ጨረታው በዚሁ ዕለት በ 4፡30 ጠዋት ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በድርጅቱ የመሰብሰቢያ አዳራሽ ይከፈታል፡፡ ከላይ የተጠቀሱትን መስፈርቶች ያላሟላ ተጫራች ያለተጨማሪ ማስታወቂያ ክውድድሩ ወጪ ይደረጋል።
ድርጅቱ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
አድራሻ፡- ቦሌ መንገድ ደንበል የገበያ ማዕከል ጀርባ በሚገኘው የድርጅቱ
ዋና መ/ቤት ህንፃ 5ኛ ፎቅ
ስልክ ቁጥር 011-1-569992
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ
ኮሜርሻል ኖሚኒስ ኃ.የተ.የግ.ማ
