የከሚሴ ከተማ አስተዳደር ገንዘብ ጽ/ቤት በከተማ አስተዳደሩ እና በፖሊስ ጣቢያ ግቢ ውስጥ የሚገኙ ያገለገሉ እቃዎችን ማለትም የመኪና ባትሪና መለዋወጫ እቃዎች፣ ብረታ ብረቶች፣ ስከራፕ ያደረጉ የመኪና አካሎች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል።
ያገለገሉ የመኪና ባትሪና ስፔሮች፣ ብረታ
ብረቶች፣ ስክራፕያደረጉ የመኪና አካሎች ሽያጭ
ብሄራዊ ግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ
የከሚሴ ከተማ አስተዳደር ገንዘብ ጽ/ቤት በከተማ አስተዳደሩ እና በፖሊስ ጣቢያ ግቢ ውስጥ የሚገኙ ያገለገሉ እቃዎችን ማለትም የመኪና ባትሪና መለዋወጫ እቃዎች፣ ብረታ ብረቶች፣ ስከራፕ ያደረጉ የመኪና አካሎች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል።
ስለሆነም በጨረታው ለመሳተፍ ፍቃደኛ የሆኑ
1. የጨረታው ሰነድ ከከሚሴ ከተማ አስተዳደር ገንዘብ ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 7 በግዢ/ፋይ/ንብ/አስ/ዋና የስራ ሂደት ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ዕለት ጀምሮ ለ 15 ተከታታይ ቀናት ስለሚቆይ ለሰነዱ የማይመለስ የኢትዮ. ብር 200 /ሁለት መቶ ብር/ ብቻ በመክፈል የጨረታ ሰነዱን መውሰድ ይችላሉ።
2. ተጫራቾች የጨረታውን ሰነድ ዋናውን በታሸገ ኤንቨሎፖች በአብክመ የከሚሴ ከተማ አስተዳደር ገንዘብ ጽ/ቤት በግዢ/ፋይ/ንብ/አስ/ዋና የስራ ሂደት ለዚሁ ተግባር በተዘጋጀው ሣጥን ውስጥ ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ አስራ ስድስት /16/ ቀን ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት እስከ 4፡00 ሰዓት ድረስ ባለው ጊዜ ማስገባት ይኖርባቸዋል።
3. ጨረታው በቀን 19/08/2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡30 ላይ በግዢ/ፋይ/ንብ/አስ/ዋና የስራ ሂደት ቢሮ ተጫራቾች ወይንም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል።
4. መሥሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉ ወይንም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
5. ተጨማሪ ማብራሪያ ከፈለጉ፤ በከሚሴ ከተማ አስተዳደር ገንዘብ ጽ/ቤት በግንባር በመቅረብ ወይንም በስልክ ቁጥር 033 554 0144 ደውለው መረዳት ይችላሉ።
የከሚሴ ከተማ አስተዳደር ገንዘብ ጽ/ቤት
