የደ/ም/ኢ/ህ/ክ/መ/ባ/ቱ/ስፖርት ቢሮ በ2018 ዓ.ም በጨረታ መለያ ቁጥር ግ.ጨ ባ/ቱ/ስ01/18 ለሚዛን አማን ስፖርት አካዳሚ የጅምናዝየም ስፖርት ዕቃዎች በግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ ህጋዊ ፍቃድ ካላቸዉ ድርጅቶች እና ነጋዴዎች አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
በድጋሚ የወጣ የስፖርት ጅምናዝየም ዕቃዎች
ግዥ ማስታወቂያ
የደ/ም/ኢ/ህ/ክ/መ/ባ/ቱ/ስፖርት ቢሮ በ2018 ዓ.ም በጨረታ መለያ ቁጥር ግ.ጨ ባ/ቱ/ስ01/18 ለሚዛን አማን ስፖርት አካዳሚ የጅምናዝየም ስፖርት ዕቃዎች በግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ ህጋዊ ፍቃድ ካላቸዉ ድርጅቶች እና ነጋዴዎች አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
የዕቃዎች ዝርዝር................................................... የጨረታ ማስከበሪያ ብር መጠን
ምድብ -- የጅምናዝየም ስፖርት ዕቃዎች...................................................ብር 50,000.00
በጨረታው የሚወዳደሩ ተጫራቾች ማሟላት የሚገባቸው መስፈርቶች፡-
1. በሚወዳደሩበት ዘርፍ የዘመኑ ግብር የተከፈለበት ሕጋዊ የንግድ ፈቃድ፣ የምዝገባ ምስክር ወረቀት፣ የቫት ተመዝጋቢ ስለመሆናቸው ማረጋገጫ፣ የግብር ከፋይ መለያ TIN ሰርተፊኬት፣ እና በጨረታ መሳተፍ የሚያስችል የድጋፍ ደብዳቤማቅረብ ይኖርባቸዋል።
2. ተጫራቾች በሚወዳደሩበት ጨረታ በንግድ ዘርፍ ያላቸውን ሰነዶች ኮፒዉንና እንዲሁም ቢሮ ባዘጋጀው ኦርጅናል ጨረታ ሠነድ ላይ ዋጋ በመሙላት ኦርጅናሉንና ኮፒዉን በፖስታ አሽጎ ማቅረብ ይጠበቅበታል።
3. ተጫራቾች በጨረታው ለመካፈል የጨረታ ማስከበሪያ ቢድ ቦንድ በባንክ በተመሰከረ የባንክ ጋራንቲ ወይም CPO በተጠየቀው ገንዘብ መጠን ማስያዝ ይኖርባቸዋል።
4. ተጫራች ድርጅቶች የጨረታ ሰነዱን ማስታወቂያው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 15ኛ ቀን ከጧቱ 4፡00 ሰዓት ድረስ ዘውትር በሥራ ሰዓት በኢት ንግድ ባንክ አካውንት ቁጥር 1000454317754 ደ/ምዕ/ኢ//ህ/ክ/መ/ባ/ቱ/ስፖርት ቢሮ ስም የማይመለስ ብር 400.00 (አራት መቶ ብር) በመክፈል ኦርጅናል የባንክ ስሊፕ ይዘዉ በመምጣት ከቢሮ ግ/ፋይ/ን/አስ/ር ዳይሬክቶሬት ቢሮ በመቅረብ መውሰድ ይችላሉ።
5. ጨረታው በ15ኛዉ ቀን ከጧቱ 4፡00 ሰዓት ተዘግተዉ በዕለቱ 4፡30 ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸዉ በተገኙበት ደ/ምዕ/ኢ/ህ/ክ/መ/ባ/ቱ/ስፖርትቢሮ ይከፈታል።
6. ሁሉም ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ ያስያዙት CPO/ ባንክጋራንቲ የሚመለስላቸው አሸናፊ ድርጅቶች ውሉን ሲፈራረሙና የውል ማስከበሪያ 10% CPO ሲያሲይዙ ይሆናል።
7. አሸናፊ ተጫራች ዕቃዉን እስከቦታው በማምጣት ገጥሞ የሚያስረክብ ይሆናል።
8. ቢሮ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 09 39 12 62 16/ 09 17 83 17 15 መጠየቅ ይቻላል።
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልላዊ መንግስት
የባህል ቱሪዝምና ስፖርት ቢሮ
