ጋሞ/ህ/ብ/ክ/መ/ጤና ቢሮ ከዚያ በታች የተዘረዘሩትን ግንባታዎች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል።
ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ
ሎት 1. በላሬ ወረዳ የኩርኝጉች ጤና ጣቢያ ግንባታን በደረጃ 5 BC/GC እና ከዚያ በላይ ሎት2. በአበቦ ወረዳ የመንደር 8/9 ጤና ጣቢያ የባለሙያ መኖሪያ ቤት ግንባታን በደረጃ 5 BCIGC እና ከዚያ በላይ ሎት 3. በጎደሬ ወረዳ የጌለሻ ኮምፕሪሄንሲቭ ጤና ኬላ ግንባታን በደረጃ 5 BC/GC እና ከዚያ በላይ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል። በዚሁ መሰረት ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች ሟሟላት ይጠበቅባችኋል።
1. የዘመኑ የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያለው
2. የተጨማሪ እሴት ታክስ የምዝገባ የምስክር ወረቀት ያለው
3. የዘመኑን ግብር የከፈሉ ለመሆናቸው ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ
4. ጨረታው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 ተከታታይ የስራ ቀናት ተጫራቾች ለዚሁ የተዘጋጀውን የጨረታ ዶክመንት /ሰነድ/ የማይመለስ ብር 2,000 /ሁለት ሺህ ብር/ በመክፈል ከክልሉ ጤና ቢሮ ግዥና ፋይናንስ ዳይሬክቶሬት ክፍል መግዛት ይቻላሉ፡፡
5. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና (ቢድ ቦንድ) ብር ለሎት አንድ፣ 250,000 /ሁለት መቶ ሃምሳ ሺህ ብር/፣ ለሎት ሁለት 100,000 /አንድ መቶ ሺህ ብር/፣ ለሎት ሶስት 200,000 /ሁለት መቶ ሺህ ብር/፣ በባንክ የተረጋገጠ ሲፒኦ ወይም በሁኔታ በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ ባንክ ጋራንት⁄ ወይም ከታወቀ ባንክ የክፍያ ማዘዣ ቼክ ከጨረታ ሰነዶቻቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
6. የጨረታው ቴከኒካል ሰነድ አንድ ኦርጅናል አንድ ኮፒ ተሞልቶ እያንዳንዱ በሰም በታሸገ ካኪ ፖስታ ተደርጎ <<ቴክኒካል ሰነድ ኦርጅናል>> እና <<ቴክኒካል ሰነድ ኮፒ›› ተብሎ መለየት የሚኖርበት ሲሆን በተመሳሳይ መልኩ ፋይናንሻል ሰነዱም እንድ ኦርጅናል እና አንድ ኮፒ ተሞልቶ እያንዳንዱ በሰም በታሸገ ካኪ ፖስታ ተደርጎ <<ፋይናንሻል ሰነድ ኦርጅናል› እና <<ፋይናንሻል ሰነድ ኮፒ ተበሎ መለየት ይኖርበታል። ሁሉንም በአንድ እናት ፖስታ በማደረግ በ16ኛው ቀን እስከ ጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ድረስ ለዚሁ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ አስገብተው ጠዋት 4፡00 ሰዓት ታሽጎ በዚሁ ቀን በ4፡30 ሰዓት ላይ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው ባሉበት በከልሉ ጤና ቢሮ ይከፈታል።
7. ቢሮው የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
8. የጨረታ መክፈቻ ቀኑ ቅዳሜ እና እሁድ ወይም የህዝብ በዓላት ቀን ከሆነ በቀጣዩ የስራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ይከፈታል።
9. ተጨማሪ መረጃ ቢያስፈልግ በስልክ ቁጥር 0475510537 እና 04755138 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ።
ጋሞ/ህ/ብ/ክ/መ/ጤና ቢሮ
