Tender Detail

Tender Details


ወጋገን ባንክ በአዋጅ ቁጥር 1147/2011 መሰረት ከዚህ በታች የቀረቡትን የመያዣ ንብረቶች በግልጽ የሐራጅ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡


                                           ወጋገን ባንክ አ.ማ

                        ለመጀመሪያ ጊዜ የወጣ የሀራጅ ጨረታ ማስታወቂያ

                              ቁጥር፡ ወጋገን 023/2018

       ወጋገን ባንክ በአዋጅ ቁጥር 1147/2011 መሰረት ከዚህ በታች የቀረቡትን የመያዣ ንብረቶች በግልጽ የሐራጅ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡

          

ተ.ቁ የተበዳሪው ስም ንብረት አስያዥ አበዳሪ

ቅርንጫፍ

የተሽከርካሪ            ዓይነት የሰሌዳ ቁጥር የሻንሲ/ሴሪያል/ ቁጥር የሞተር

ቁጥር

ዘመን የነዳጅ

አይነት

የጨረታ መነሻ        ዋጋ ጨረታው የሚከናወንበት ቀን
ቀን ሰዓት
1 ኤን ኬ ኤች ኮንስትራክሽን ኃ/የተ/የግ/ማ/ ተበዳሪው ሰባራ ባቡር ድርብ ተግባር አአ-03-B33009 MR0DB9CD7M5151328 2GD-5010093 2021 ናፍጣ 7,200,000.00  

ግንቦት

13/2018     ዓ.ም

 

ከጧቱ 3፡00-6፡00 ሰዓት

2 አቶ አማኑኤል አብርሃ ተበዳሪው ባምቢስ ድርብ ተግባር አአ-03-A29336 MROKOB8C0G1111217 2GD-0042332 2016 ናፍጣ 6,000,000.00

 

ማሳሰብያ

  1. ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው የጨረታ መነሻ ዋጋ ¼ (አንድ አራተኛ) በባንክ የተረጋገጠ የክፍያ ሰነድ (C.P.O) በወጋገን ባንክ አ.ማ ስም በማሰራት በጨረታው ዕለት በመቅረብና በመመዝገብ በጨረታው ላይ መሳተፍ ይችላሉ፡፡
  2. የጨረታ አሸናፊ ከባንኩ የብድር ማስመለስ ዳይሬክቶሬት ማሸነፉን የሚገልጽ ደብዳቤ ከተሰጠው ቀን ጀምሮ ቀሪውን ገንዘብ በ15 /አስራ አምስት/ ቀናት ውስጥ አጠናቆ መክፈል ይኖርበታል፡፡ ባይከፍል ግን የሐራጁ ውጤት ተሰርዞ ያስያዘው ገንዘብ ለባንኩ ገቢ ይሆናል፣ ላላሸነፉት ተጫራቾች ግን ያስያዙት ሲፒኦ ወዲያዉኑ ይመለስላቸዋል፡፡
  3. በጨረታው አሸናፊ ለሆነ፤ የባንኩን የብድር ፖሊሲ፤ መመሪያ እና ቅድመ ሁኔታ ለሚያሟላ ተጫራች ባንኩ በውስጥ መመሪያ መሰረት ብድር ሊያመቻች ይችላል፡፡
  4. የተጫራቾች የምዝገባ ሰዓት፤ ከጧቱ 3፡00 – 4፡00 ሰዓት ድረስ ብቻ ሲሆን ምዝገባው ከተጠናቀቀ በኋላ ለእያንዳንዱ ንብረት የሚመደበው የጥሪ ሰዓት 30 ደቂቃ ብቻ ነው፡፡ ሆኖም የጨረታው መጠናቀቂያ ሰዓት ድረስ አሸናፊው ካልተለየ አሸናፊ እስኪለይ ድረስ ጨረታው ይቀጥላል፡፡
  5. በጨረታው የተሻለ ዋጋ ያቀረበ ተጫራች ጨረታውን ካካሄደው ከባንኩ የብድር ማስመለስ ዳይሬክቶሬት ማሸነፉን የሚገልጽ ደብዳቤ ሲደርሰው ብቻ አሸናፊ ይባላል፡፡
  6. ንብረቱ በገዢው ስም እንዲዞር ባንኩ ለሚመለከተው መንግስታዊ አካል ደብዳቤ ይጽፋል፡፡
  7. ጨረታው የሚካሄደው፡ በወጋገን ባንክ ዋና መስርያ ቤት 13ኛ ፎቅ ባለው የመሰብሰብያ አዳራሽ ይሆናል፡፡
  8. ለሀራጅ ጨረታ የቀረቡትን ንብረቶች ለመጎብኘት የሚፈልግ ተጫራች የጨረታው ቀን ከመድረሱ ከ7 የሥራ ቀናት በፊት ከባንኩ ጋር ቀጠሮ በማስያዝ መጎብኘት ይችላል፡፡
  9. ተበዳሪው /ንብረት አስያዥ/ ወይም ሁለቱም በጨረታው ቀን እና ሰዓት በቦታው ላይ መገኘት ይችላሉ፡፡ ነገር ግን ተበዳሪው /ንብረት አስያዡ/ በጨረታ ቀን እና ሰዓት በቦታው ባይገኝ ጨረታው በሌለበት ይካሄዳል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ጨረታው ላይ መገኘት የሚችሉት ተጫራቾች ወይም የተጫራቾች ህጋዊ ተወካዮች ብቻ ናቸው፡፡
  10. ማንኛውንም ለመንግስት ሊከፈል የሚገባውን ክፍያ ሙሉ በሙሉ የጨረታው አሸናፊ የሚከፍል ይሆናል፡፡
  11. ለበለጠ ማብራሪያ ወይም የጉብኝት ቀጠሮ ለማመቻቸት ወጋገን ባንክ አ.ማ የብድር ማስመለስ ዳይሬክቶሬት 011-558-18-37፣
  12. ባንኩ የተሻለ መንገድ ካገኘ በጨረታው አይገደድም፡፡

 

ወጋገን ባንክ አ.ማ

Save Tender