ድርጅታችን ኮሜርሻል ኖሚኒስ ኃ/የተ/የግል ማህበር ለተቋሙ አገልግሎት የሚውል ሎት 1- CCTV Surveillance System for warehouse እና ሎት 2- ፕሮጀክተር (Projector) እና ሎት 3. ልዩ ልዩ የጽዳት መሳሪያዎች (Window squeezer, window applicator Telescopic pole... ወዘተ.) በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ግዢ ለመፈጸም ይፈልጋል፡፡
የጨረታ ማስታወቂያ
CN/NCB/35/18 እና CN/NCB/36/18
ድርጅታችን ኮሜርሻል ኖሚኒስ ኃ/የተ/የግል ማህበር ለተቋሙ አገልግሎት የሚውል፡-
ሎት 1- CCTV Surveillance System for warehouse
ሎት 2- ፕሮጀክተር (Projector) እና
ሎት 3. ልዩ ልዩ የጽዳት መሳሪያዎች (Window squeezer, window applicator Telescopic pole... ወዘተ.) በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ግዢ ለመፈጸም ይፈልጋል፡፡ በመሆኑም ተጫራቾች የታደሰ የንግድ ፈቃድ፣ በጨረታ ላይ መሳተፍ እንደሚችሉ የሚገልጽ ደብዳቤ፣ በአቅራቢዎች ዝርዝር ውስጥ የተመዘገቡበትን ማስረጃ፣ የቲን ቁጥር ሰርተፍኬት፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ የምዝገባ ሰርተፍኬት፣ የጨረታ ማስከበሪያ ሲ.ፒ.ኦ እና የዕቃው ዝርዝር መግለጫ በተለየ በሰም በታሸገ ፖስታ እንዲሁም ዕቃዎቹን የምታቀርቡባቸውን ዋጋ በተለየ በሰም በታሸገ ሁለተኛ ኢንቨሎፕ በማድረግ እንድትወዳደሩ ይጋበዛል፡፡ የጨረታ ዶክመንቱን ቦሌ መንገድ ደንበል የገበያ ማዕከል ጀርባ በሚገኘው የድርጅቱ ዋና መ/ቤት ህንፃ 5ኛ ፎቅ የግዢ ዋና ክፍል ብር 100.00 በመክፈል ከሰኞ እስከ አርብ (ጠዋት 2፡00-6፡00 እንዲሁም ከሠዓት 7፡00-11፡00) እንዲሁም ቅዳሜ ጠዋት 2፡00-6፡00 ሠዓት ማግኘት ይቻላል፡፡ ለሎት 1 እና 2 ጨረታ ማስከበሪያ ብር 100,000 (አንድ መቶ ሺህ ብር) ሲሆን ሎት 3 ብር 100,000 (አንድ መቶ ሺህ ብር) በባንክ በተረጋገጠ ሲ.ፒ.አ. ከመጫረቻ ዶከመንት ጋር መቅረብ ይኖርበታል፡፡
ተጫራቾች የመጫረቻ ዶክመንታቸውን ከላይ በተጠቀሰው አድራሻና የሥራ ሰዓት በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ እስከ ግንቦት 27 ቀን 2018 ዓ.ም 4፡00 ድረስ ማስገባት ይችላሉ፡፡ ጨረታው በዚሁ ዕለት በ 4፡30 ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በድርጅቱ የመሰብሰቢያ አዳራሽ ይከፈታል፡፡ ከላይ የተጠቀሱትን መስፈርቶች ያላሟላ ተጫራች ያለተጨማሪ ማስታወቂያ ከውድድሩ ውጪ ይደረጋል።
ድርጅቱ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ቦሌ መንገድ ደንበል የገበያ ማዕከል ጀርባ በሚገኘው የድርጅቱ ዋና መ/ቤት ህንፃ 5ኛ ፎቅ
ስልክ ቁጥር፡- 011-1-569992
አዲስ አበባ
ኮሜርሻል ኖሚኒስ ኃ.የተ.የግ.ማ
