የኮልፌ ቅዱስ ራጉዔል አዲስ ሕይወት አ/ማህበር ባስገነባው የገበያ ማዕከል ህንጻ ውስጥ የቢሮ ፓርቲሽኖችን በመስታወት እና ሌሎች ተዛማጅ ሥራዎችን ከዚህ በታች የተገለፁትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾችን አወዳድሮ ለማሰራት ይፈልጋል፡፡
የቢሮ ፓርቲሽን ሥራ የጨረታ ማስታወቂያ
የኮልፌ ቅዱስ ራጉዔል አዲስ ሕይወት አ/ማህበር ባስገነባው የገበያ ማዕከል ህንጻ ውስጥ የቢሮ ፓርቲሽኖችን በመስታወት እና ሌሎች ተዛማጅ ሥራዎችን ከዚህ በታች የተገለፁትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾችን አወዳድሮ ለማሰራት ይፈልጋል፡፡
1. በአልሙኒየም ሥራ እና ደረጃ 5 ጠቅላላ ወይም በህንጻ ሥራ ተቋራጭ የ2018 ዓ.ም የታደሰ ህጋዊ ንግድ ፍቃድ እና የንግድ ምዝገባ ሰርተፊኬት፡፡
2. የቫት እና የግብር ከፋይነት ሰርተፊኬት (TIN)፡፡
3. የ2017 ዓ.ም ከግብር ዕዳ ነፃ የሆኑበትን ሰርተፊኬት፡፡
4. ለሚቀበሉት ክፍያዎች ህጋዊ ደረሰኝ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
5. በዘርፉ ተሰማርተው ለሰሩት ሥራ በቂ የሥራ ልምድ ማቅረብ እና የሰሩትን ሥራም ማሳየት የሚችሉ።
ከላይ የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾች የሰነዳቸውን ኦርጅናል እና ኮፒ በመያዝ ዋጋ ማቅረቢያ ሰነዱን ከማህበሩ ጽ/ቤት ብር 1,000 ከፍለው በመውሰድ ዋጋቸውን ሞልተው ለጨረታ ማስከበርያ ብር 20,000.00 (ሃያ ሺህ ብር) በሲፒኦ ብቻ በማያያዝ በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 15 ተከታታይ የሥራ ቀናት ውስጥ ከታች በተገለፀው ሰዓት የሰነዶቻቸውን አንድ ኦርጅናል እና አንድ ኮፒ በመያዝ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይችላሉ፡፡
ጨረታው ከወጣበት ቀን አንስቶ በአስራ አምስተኛው ቀን 8፡00 ሰዓት ተዘግቶ ከቀኑ 9፡00 ሰዓት ላይ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በአ/ማህበሩ ጽ/ቤት ይከፈታል። አክሲዮን ማህበሩ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው። ቅናሽ ዋጋ የመምረጥ ግዴታም የለበትም፡፡
ማስታወሻ፡-
· አድራሻ፡- ኮልፌ አጠና ተራ ከቴሌው ጀርባ የኮልፌ ቅዱስ ራጉዔል አዲስ ሕይወት አ/ማህበር ብሎክ 2 አራተኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 4
· የጨረታውን ሰነድ መውሰድ የሚቻለው ከጠዋት 2፡30 እስከ 6፡30 ከሰዓት 7፡30 እስከ 10፡30 ብቻ ይሆናል
· ስልክ 09-32-08-03-77 ወይም 09-12-05-47-92
የኮልፌ ቅዱስ ራጉዔል አዲስ ሕይወት አ/ማህበር
