Tender Detail

Tender Details


በጉምሩክ ኮሚሽን የኮምቦልቻ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በተለያየ ጊዜ ውርስ የተደረጉ clipper /ቶንዶስ/፣ dorco /ምላጭ/፣ የተሽከርካሪ መለዋወጫ፣ ምግብ እቃዎች፣ ኤሌክትሮኒክስ፣ አልባሳት፣ Mosquito net /አጎበር/ እና ኮስሞቲክስ በግልፅ እንዲሁም ኮስሞቲክስ፣ ተሽከርካሪ፣ የተሽከርካሪ መለዋወጫ፣ የኤሌክትሪክ እቃዎች፣ ኤሌክትሮኒክስ፣ ጫማ፣ welding electrod እና Wovenbag በሀራጅ ጨረ


የጨረታ ማስታወቂያ

ጨረታ ቁጥር _30/2018 .

 

በጉምሩክ ኮሚሽን የኮምቦልቻ ቅርንጫፍ /ቤት በተለያየ ጊዜ ውርስ የተደረጉ clipper /ቶንዶስ/ dorco /ምላጭ/ የተሽከርካሪ መለዋወጫ፣ ምግብ እቃዎች፣ ኤሌክትሮኒክስ፣ አልባሳት፣ Mosquito net /አጎበር/ እና ኮስሞቲክስ በግልፅ እንዲሁም ኮስሞቲክስ፣ ተሽከርካሪ፣ የተሽከርካሪ መለዋወጫ፣ የኤሌክትሪክ እቃዎች፣ ኤሌክትሮኒክስ፣ ጫማ፣ welding electrod እና Wovenbag በሀራጅ ጨረታ ባሉበት ሁኔታ መሸጥ ይፈልጋል።

በመሆኑም ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የምታሟሱ ተጫራቾች መወዳደር የምትችሱ ሲሆን መስፈርቶቹ፡-

1)    በጨረታው ለመወዳደር የሚፈልግ ማንኛውም ተጫራች በጨረታ ከሚሸጠው እቃ ጋር ተዛማጅነት ያለው የፀና የንግድ ፈቃድ፣ ተጨማሪ ዕሴት ታክስ ምዝገባ ሰርትፍኬት፣ የዘመኑን ግብር የከፈለ ለመሆኑ ከግብር /ቤት የሚሰጥ የምስክር ወረቀት (ክሊራንስ) እና የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ማቅረብ የሚችል ሲሆን ተሽከርካሪ መጫረት ለምትፈልጉ ንግድ ፈቃድ የማይጠይቅ በመሆኑ ማንኛውም እድሜው 18-አመት በላይ የሆነ የነዋሪነት መታወቂያ ያለው ግለሰብ መጫረት ይችላል፡፡

2)    በጨረታው ለመወዳደር የሚፈልግ ማንኛውም ተጫራች በጨረታ ከሚሸጠው እቃ ጋር ተዛማጅነት ያለው የፀና የንግድ ፈቃድ፤ ተጨማሪ ዕሴት ታክስ ምዝገባ ሰርትፍኬት፣የዘመኑን ግብር የከፈለ ለመሆኑ ከግብር /ቤት የሚሰጥ የምስክር ወረቀት (ክሊራንስ) እና የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ማቅረብ የሚችል ግለሰብ መጫረት ይችላል።

3)    የዚህ አንቀፅ ተራ ቁጥር (1) ድንጋጌ ቢኖርም ግምታዊ ዋጋው ከብር 2 ሚሊዮን በታች የሆነ ማንኛውንም እቃ ለመግዛት የተጨማሪ እሴት ታክስ ምዝገባ የምስክር ወረቀት (ሰርተፍኬት) ማቅረብ አያስፈልገውም።

4)    በጨረታ የሚሸጠው እቃ በኮሚሽኑ ቁጥጥር ስር ከመግባቱ በፊት ባለቤት የነበረ ወይም የባለቤቱ ወኪል ወይም ቤተሰብ የሆነ ሰው በማንኛውም መልኩ በጨረታው መሳተፍ አይችልም።

5)    ተጫራቾች የእቃዎቹን ዝርዝር፤ አይነትና ብዛት የጨረታ ሰነድና መመሪያ እንዲሁም የጨረታ ዋጋ ማቅረቢያ ቅፅ የማይመለስ ብር 100 (አንድ መቶ) እየከፈሉ ኮምቦልቻ ቅርንጫፍ /ቤት ማስታወቂያው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ ስድስተኛው (6) ቀን 300 ሰዓት ድረስ መግዛት ይችላሉ።

6)    ተጫራቾች ለግልፅ ጨረታው የእቃዎችን ዝርዝር በያዘው ሰነድ ላይ ተጫራቹ የሰጠው ዋጋ በሚለው አምድ ሥር የሚገዙበትን ዋጋ በአሀዝና በፊደል ገልፀው እና በተራ ቁጥር 1 ላይ የተገለፁትን በኤንቨሎፕ ወይም በፖስታ በማሸግ ጉምሩክ ኮሚሽን ኮምቦልቻ ቅርንጫፍ /ቤት በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስታወቂያው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ ስድስተኛው ቀን 350 ሰዓት ድረስ ማስገባት አለባቸው።

7)    የጨረታ ማስታወቂያው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት በስድስተኛው ቀን በጉምሩክ ኮሚሽን ኮምቦልቻ //ቤት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት የሚካሄድ ሲሆን ግልፅ ጨረታው 350 ሰዓት ተዘግቶ 400 ሰዓት የሚከፈት ሲሆን ሐራጅ ጨረታው 430 ሰዓት የሚጀመር ይሆናል።

8)    ተጫራቾች በጨረታው አሸናፊ መሆናቸው ከተገለፀበት ቀን ጀምሮ 05 ተከታታይ የስራ ቀናት ውስጥ ያሸነፉበትን ዋጋ በመክፈል ንብረቶቹን ማንሳት ይኖርባቸዋል። በተሰጠው የጊዜ ገደብ ከፍለው የማይወስዱ ተጫራቾች ያስያዙት የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና (CPO) ለመ/ቤቱ ገቢ ተደርጎ እቃዉ እንደገና ለጨረታ ይቀርባል።

9)    ተጫራቾች ለእቃዎች በሚያቀርቡት የመጫረቻ ዋጋ አሸናፊ ከሆነ ተጨማሪ ዕሴት ታክስ 15% (VAT) የሚጨመርበት ይሆናል።

10) ተጫራቾች ጨረታው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ ስድስተኛው ቀን ድረስ ለሽያጭ የተዘጋጁ እቃዎችን በኮምቦልቻ ጉምሩክ //ቤት በስራ ሰዓት ከጠዋቱ 300 ሰዓት እስከ 600 ሰዓት ከሰዓት በኋላ 8፡ዐዐ ሰዓት እስከ 1000 ሰዓት ድረስ እና ስድስተኛው ቀን ጠዋት 300 ሰዓት ድረስ መመልከት ይችላሉ።

11)   ተጫራቾች ለግልፅ ጨረታ እቃዎች የሰጡትን የመግዣ ዋጋ አምስት በመቶ (5%) እና ለሀራጅ ጨረታ የእቃው መነሻ ዋጋ 2 ሚሊዮን ብር በላይ ለሆነ እቃ የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና 200,000 (ሁለት መቶ ሺህ) ብር እንዲሁም የእቃው መነሻ ዋጋ 2 ሚሊዮን ብር በታች ለሆነ እቃ የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና 100,000 (መቶ ሺህ) ብር የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና በባንክ የተረጋገጠ ሲፒኦ (CPO) ከዋጋ ማቅረቢያ ቅፅ ጋር ማቅረብ አለባቸው።

12)    መስሪያ ቤቱ ጨረታውን በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።

 

ለተጨማሪ ማብራሪያ በስልክ ቁጥር 033 551 06 93 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ።

 

በጉምሩክ ኮሚሽን ኮምቦልቻ ቅርንጫፍ /ቤት

Save Tender