Tender Detail

Tender Details

  • Company መቄዶንያ የበጎ አድራጎት ማህበር
  • Address አዲስ አበባ ከተማ ወረዳ 03 በተለምዶ አያት ኮንዶሚኒየም ከጠበል መድኃኒአለም ቤተ ክርስቲያን ፊት ለፊት : አዲስ አበባ ፡ ኢትዮጵያ, Phone: 0930796413
  • Website
  • Deadline28 Jun 2026, 10:30 AM
  • magazineአዲስ ዘመን
  • Bid Document Price500.00
  • opening date2026-06-29 11:00:00
  • Categories Vehicle

መቄዶንያ የበጎ አድራጎት ማኅበር ያገለገሉ የተለያየ ሞዴል ያላቸው ሠነድ ያላቸውና የሌላቸው 18 ተሽከርካሪዎችን በጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡


የጨረታ ማስታወቂያ

ጨረታ ቁጥር 126

 

መቄዶንያ የበጎ አድራጎት ማኅበር ያገለገሉ የተለያየ ሞዴል ያላቸው ሠነድ ያላቸውና የሌላቸው 18 ተሽከርካሪዎችን በጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡

ተሽከርካሪዎቹን ለመግዛት የሚፈልግ ማንኛውም ተጫራች አዲስ አበባ ከተማ፣ ለሚ ኩራ /ከተማ፣ ወረዳ 03 (በተለምዶ አያት ኮንዶሚኒየም፣ ከፀበል መድኃኒዓለም ቤተክርስቲያን) ፊት ለፊት በሚገኘው በማዕከሉ ዋና መሥሪያ ቤት ቅጥር ግቢ ውስጥ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ 14 ቀን አየር ላይ ቆይቶ 15ኛው ቀን ከጧቱ 430 ሰዓት ተዘግቶ በዚሁ ዕለት 500 ሰዓት ተጫራቾችና ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡ ነገር ግን 15ኛው ቀን እሑድ ወይም የብሔራዊ በዓል ከሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀን ይሆናል፡፡

·        ለጨረታው የተዘጋጁትን ተሽከርካሪዎች በአዲስ ዘመን ጋዜጣ በወጣ 8ኛው ቀን ጀምሮ ከጧቱ 200 ሰዓት እስከ 1100 ሰዓት ድረስ በአካል መመልከት ይቻላል፡፡

·        የጨረታውን ሰነድ ብር 500.00 (አምስት መቶ ብር) ብቻ በመክፈል መውሰድ ይችላሉ፣

·        ሰነዱ የተጫራቾች መመሪያ በዝርዝር አካቶ የያዘ ስለሆነ ፎርሙ ከመሞላቱ አስቀድሞ በጥንቃቄ ሊነበብ ይገባል፡፡

·        የጨረታ ሰነዱ በማዕከሉ ቅጥር ግቢ ውስጥ ለሽያጭ የተዘጋጁትን ተሽከርካሪዎች ዝርዝር እና የጨረታ ማስገቢያ ፎርም የያዘ ሲሆን እየተዘዋወሩ ከተመለከቱ በኋላ ለመግዛት የሚወስኑትን ተሽከርካሪ ይለያሉ፣ ስሙንና የሠሌዳ/ኮድ ቁጥሩን ይይዛሉ፡፡

·        ለእያንዳንዱ ተሽከርካሪ የጨረታ ማስከበሪያ (ማስያዣ) የሞሉትን ዋጋ 10% ሲፒኦ CPO ማሲያዝ ይኖርባቸዋል፡፡

·        ተጫራቾች የሚገዙበትን ዋጋ በጨረታ ሰነዱ ፎርም ላይ በመሙላት እና የጨረታ ማስከበሪያ በባንክ ከተረጋገጠ ሲፒኦ ጋር አያይዘውና በታሸገ ኤንቨሎፕ አድርገው ለዚህ ተብሎ በተዘጋጀው ሣጥን ውስጥ ጨረታው በይፋ ሊከፈት ግማሽ ሰዓት እስከሚቀረው ድረስ ማስገባት ይችላሉ፡፡

·        ጨረታው 15ኛው ቀን ከረፋዱ 500 ሰዓት በማዕከሉ የስብሰባ አዳራሽ ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡

 

ማዕከሉ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሠረዝ መብቱ በሕግ የተጠበቀ ነው፡፡

 

ለበለጠ ማብራሪያ በስልክ ቁጥር 0936019191) ወይም 0975264159 መጠየቅ ይቻላል፡፡

 

መቄዶንያ የበጎ አድራጎት ማኅበር

 

Save Tender