የመከላከያ ሰራዊት ፋውንዴሽን ለሚያስገነባቸው የሠራዊቱ የጋራ መኖሪያ ቤቶች ግንባታ ለጋሻ ፕሮጀክት አገልግሎት የሚውል ከዚህ በታች የተገለፁትን Electric Materials በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
ግልፅ ጨረታ ማስታወቂያ
ቁጥር መሰፋ/ብ/ግ/ጨ/019/2018
የመከላከያ ሰራዊት ፋውንዴሽን ለሚያስገነባቸው የሠራዊቱ የጋራ መኖሪያ ቤቶች ግንባታ ለጋሻ ፕሮጀክት አገልግሎት የሚውል ከዚህ በታች የተገለፁትን Electric Materials በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
· Electric copper power cables and wire
በዚህም መሠረት ተጫራቾች ከዚህ በታች የተገለፁትን መስፈርቶች በማሟላት በጨረታው የምትሳተፉ መሆኑን እንገልፃለን፡፡
1. ተጫራቾች በዘርፉ ህጋዊ የንግድ ፍቃድ ያላቸው፤ የዘመኑን ግብር የከፈሉ VAT Registration Certeficate/ በገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር የተመዘገቡ እና የቲን ሰርተፊኬት የብቃት ሰርተፊኬት Tax clearance certificate የመንግሰት የግዥ እና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ ሰርተፊኬት ማቅረብ አለባቸው።
2. ተጫራቾች ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ላይ ከወጣበት ዕለት ጀምሮ ዘወትርበስራ ሰዓት የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር 500.00 (አምስት መቶ ብር ብቻ) በመክፈል መ/ሰ/ፋ ግዥ ቡድን ክፍል ቢሮ ቁጥር 015 ድረስ በመቅረብ መውሰድ ይችላሉ፡፡
3. ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ማለትም ብር 250,000 /ሁለት መቶ ሃምሳ ሺህ ብር ብቻ/ በባንክ በተመሰከረለት /ሲ.ፒ.ኦ/ በሁኔታ ላይ ያልተመሰረት የባንክ ጋራንቲ ብቻ በመከላከያ ሰራዊት ፋውንዴሽን ስም ከጨረታው ኦርጅናል ቴክኒካል ሰነድ ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፡፡
4. ተጫራቾች ለሚጫረቱባቸው ፋይናንሺያል እና ቴክኒካል ሰነዶቻቸውን ኦሪጂናል እና አንድ ኮፒ ለየብቻ ተለይቶ በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ 15 ተከታታይ ቀናት ቢሮ ቁጥር 015 በመምጣት መሥሪያ ቤቱ ባዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይችላሉ። እንዲሁም ተያያዥ ዶክመንቶች ማቅረብ አለባቸው።
5. ይህ ጨረታ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 ተከታታይ ቀናት አየር ላይ ውሎ በ16ኛው ቀን ልክ 8፡00 ሰአት ላይ የጨረታ ሳጥኑ ታሽጎ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በእለቱ ከጠዋቱ 8:30 መ.ሰ.ፋ ግዥ ቡድን ይከፈታል፡፡
6. የጨረታ አሸናፊዎች ማሸነፋቸው በጽሁፍ የሚገለጽላቸው እና የውል ስምምነት የሚፈፅሙ ይሆናል።
7. በጨረታ ያላሸነፉ ድርጅቶች ያስያዙት የጨረታ ማስከበሪያ ወዲያውኑ ይመለስላቸዋል።
8. ፋውንዴሽኑ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ለበለጠ መረጃ
አድራሻ፡- አዲስ አበባ ከሜክሲኮ ወደ ቄራ በሚወስደው ላንድ ማርክ ሆስፒታል አጠገብ
ስልክ ቁጥር፡- 0115572752
መከላከያ ሰራዊት ፋውንዴሽን
