የመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ ለሀረር ፈዴራል ፖሊስ ሆስፒታል እና አፓርትመንት ፕሮጀከት ግንባታ አገልግሎት የሚውል የ Supply and Fix Satellite dish system ግዥ ለመፈፀም ተጫራቾችን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል ::
የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር DC/ SF/84/2026
የመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ ለሀረር ፈዴራል ፖሊስ ሆስፒታል እና አፓርትመንት ፕሮጀከት ግንባታ አገልግሎት የሚውል የ Supply and Fix Satellite dish system ግዥ ለመፈፀም ተጫራቾችን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል ::
|
የዕቃው አይነት |
የፕሮጀክት ስም |
የጨረታው አይነት |
የጨረታ ቁጥር መዝጊያ ቀን እና ሰዓት |
የጨረታ ቁጥር መክፈቻ ቀን እና ሰዓት |
ጨረታ ማስከበሪያ |
|
Supply and Fix Satellite dish system |
ለሀረር ፈዴራል ፖሊስ ሆስፒታል አፓርትመንት ፕሮጀክት |
DCE/ SF/84/2026 |
ሀምሌ 1/2018 ዓ.ም 4፡00 ሰዓት |
ሀምሌ 1/2018 ዓ.ም 4፡15 ሰዓት |
100,000.00 |
ስለሆነም -
- ተጫራቾች በዘርፉ የተሰማሩ መሆኑን የሚገልፅ የታደሰ የንግድ ፈቃድ የምስከር ወረቀት ፣ የተጨማሪ እሴት ታከስ የተመዘገቡበት የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ፣ በጨረታ ለመሳተፍ የሚሰጥ የታደሰ የምስከር ወረቀት ( ታክስ ከሊራንስ ) እና የሀገር ውስጥ ተጫራቾች በአቅረቢዎች ዝርዝር ውስጥ የተመዘዘገቡ መሆኑን ሚያረጋግጥ ኮፒ ወዘተ... ማቅረብ የሚችሉ መሆን አለባቸው።
- ተጫራቾች ከላይ በሰንጠረዡ በተገለፀው መሰረት የጨረታ ማስከበሪያ Bid Bond ማቅረብ ይኖርበታል። የጨረታ ማስከበሪያው እንደ ተጫራቹ ምርጫ በቅድመ ሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና (Unconditional bank Guarantee) ወይም በባንክ የተሰጠና የተረጋገጠ (C.P.O) ከመጫረቻ ሰነዳቸው ጋር ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
- ተጫራቾች የሚያቀርቡት ዋጋ በጨረታ ሰነድ በተዘረዘረው ዝርዝር መሰረት መሆን ይኖርበታል፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 200.00 ( ሁለት መቶ ብር) በመከፈል ዘወትር በስራ ሰዓት የግዥና አቅርቦት አስተዳደር መምሪያ ቢሮ መግዛት ይቻላል።
- ተጫራቾች የሚወዳደሩበትን የጨረታ ቴከኒካል ሰነድ እና ዋጋ በታሸገ ኢንቨሎፕ ከላይ በሰንጠረዡ በተገለፀው ቀን እና ሰዓት በኢንተርፕራይዙ የግዥና አቅርቦት አስተዳደር መምሪያ ቢሮ ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
- ጨረታው በሰንጠረዡ በተገለፀው መሰረት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በድርጅቱ መሰብሰቢያ አዳራሽ ይከፈታል።
- ኢንተርፕራይዙ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
አድራሻ፡- የመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ ቃሊቲ ቶታል ዝቅ ብሎ የቀድሞው መ.ኮ.ድ ግቢ የቀጥታ ስልክ ቁጥር 0114-40-34-34 0114-42-22-70/71/2 E-mail ९८ Info@dce-et.com የድህረ ገፅ አድራሻwww.dce-et.com
ፖ.ሳ.ቁ3414
የመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ
