በኬሚካል ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን የመግር ሲሚንቶ ፋብሪካ ከአ.አ 90 ኪ/ሜትር ርቀት ከሚገኛው ሙግር ዋናው ፋብሪካ ፣ከታጠቅ 20 ኪ/ሜ/ ርቀት እና ከኢ.አ 70 ኪ.ሜትር ርቀት ከሚገኛው ደርባ ቅርንጫፍ አሮጌ ተሽካርካሪዎችና ማሽነሪዎች፣ ጎማዎች፣ባትሪ እና ቁርጥራጭብረታ ብረት _ በጨረታ ለመሽጥ ይፈልጋል፡፡
የአሮጌ ተሽከርካሪዎችና ማሽነሪዎች፣ጎማ፣ባትሪ እና ቁርጥራጭ ብረታ ብረት ሽያጭ የጨረታ ማስታወቂያ
በኬሚካል ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን የመግር ሲሚንቶ ፋብሪካ ከአ.አ 90 ኪ/ሜትር ርቀት ከሚገኛው ሙግር ዋናው ፋብሪካ ፣ከታጠቅ 20 ኪ/ሜ/ ርቀት እና ከኢ.አ 70 ኪ.ሜትር ርቀት ከሚገኛው ደርባ ቅርንጫፍ አሮጌ ተሽካርካሪዎችና ማሽነሪዎች፣ ጎማዎች፣ባትሪ እና ቁርጥራጭብረታ ብረት _ በጨረታ ለመሽጥ ይፈልጋል፡፡በጨረታው ላይ ለመሳታፍ ከዚህ በታች የተጠቀሱትን መስፈርቶችን አሟልተው መወዳደር ይችላሉ፡፡
1ኛ/ የታደሰ የንግድ ፈቃድ ወይንም የግብር ከፋይ መለየ /ቲን/ ያላቸው መሆን ይኖርባቸዋል፡፡
2ኛ/ ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና የጠቅላለ ዋጋውን 4% በባንክ በተረጋጋጠ የክፍያ ትዕዛዝ (ሲፒኦ)ማስያዝ ይጠበቅባቸዋል፡፡
3ኛ/ ተጫራቾች ለጨረታ የቀረቡ እቃዎች በሚገኙበት ቀርቦ እስከ ጨረታው መዝጊያ ቀን ድረስ ማየት ይችላሉ፡፡
4ኛ/ ተጫራቾች ማስታወቂያው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ ጨረታ መዝጊያ ቀን ባሉት ቀናት ውስጥ ተ.እ.ታ ታከስን ጨምሮ የማይመለስ ብር 575.00 /አምስት መቶ ሰባ አምስት/ በመክፈል የጨረታ ሰነድ በመግዛት በዋጋ ማቅረቢያ ቅጽ ላይበመሙላትና የታደሰ የንግድ ፈቃድ ወይንም የግብር ከፋይ መለያ/ቲን/ ኮፒ ከጨረታ ማስከበሪያ (ሲፒኦ) ጋር በማያያዝ በታሸገ ኤንቨሎኘ ውስጥ በማድረግ ገርጂ ኢምፔሪያ ሆቴል የነበረ ህንፃ በሚገኘው የማርኬቲንግ መምሪያ ቢሮ ለዚሁ በተዘጋጀው የጨረታ ሣጥን ውስጥ ሐምሌ 16 ቀን 2018 ዓ.ም ጠዋቱ 3፡30 ሰዓት ድረስ ዘወትር በሥራ ሰዓት ብቻ ማስገባት አለባቸው፡፡
5ኛ/ ጨረታው ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ሐምሌ 16 ቀን 2018 ዓ.ም ከጥዋቱ በ4፡00 ሰዓት በማርኬቲንግ መምሪያ ቢሮ ይከፈታል፡፡
6ኛ/ የጨረታው ሣጥን ከተዘጋ በኋላ ዘግይቶ የሚመጣ ተጫራች የጨረታ ሠነዱ ተቀባይነት አይኖረውም፡፡
7ኛ/አንድ ተጫራች ለጨረታ ለቀረቡ እቃዎች ለሁሉም ወይንም ለተወሰነ መጫረት ይችላል፡፡ ለተጨማሪ መረጃ
*አዲስ አበባ ገርጂ ኢምፔሪያ ሆቴል የነበረ ህንፃ በሚገኘው የማርኬቲንግ መምረያ ቢሮ በመቅረብ ወይም 0114 40 30 26/0114-40-3025 በመደወል መረጃ ማግኘት ይችላሉ፣
በኬሚካል ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን
የሙገር ሲሚንቶ ፋብሪካ
