ዘመን ባንከ አ.ማ. በቁጥር 10 ያገለገሉ ሞተር ሳይከሎችን ባሉበት ሁኔታ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል፡፡
ያገለገሉ ሞተር ሳይክሎች ሽያጭ ማስታወቂያ
(በድጋሚ የወጣ የጨረታ ማስታወቂያ)
ዘመን ባንከ አ.ማ. በቁጥር 10 ያገለገሉ ሞተር ሳይከሎችን ባሉበት ሁኔታ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል፡፡
የጨረታ ደንቦች :-
1. ሞተር ሳይከሎቹን ለመግዛት ፍላጎት ያላቸው ተጫራቾች ከሐምሌ 6 ቀን 2018 ዓ.ም እስከ ሐምሌ 20 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ዘወትር በስራ ሰዓት ሞተር ሳይከሎቹን “ጎፋ መብራት ኃይል ስኩል ኦፍ ቱሞሮ ት/ቤት” አካባቢ በሚገኘው የባንኩ ዋና መጋዘን ቅጥር ግቢ ውስጥ መመልከት ይችላሉ፤ ወይም በስልክ ቁጥር 0115-57-58-25/011 668 78 09 በመደወል ወይም ሰንጋ ተራ አካባቢ በሚገኘው በባንኩ ዋናው መስሪያ ቤት 12ኛ ፎቅ ላይ በንብረት እና ሎጂስቲክ አስተዳደር መምሪያ በአካል በመቅረብ መረጃ መጠየቅ ይችላሉ፣
2. ፍላጎት ያላቸው ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱንና የዋጋ መሙያ ቅጽ ከባንኩ የንብረት አሰተዳደርና ሎጂሰቲከሰ መምሪያ በመግዛትና እና በመሙላት በጨረታ ሰነዱ የተጠቀሰውን የጨረታ ማስከበሪያ በባንክ የተረጋገጠ የከፍያ ማዘዣ (CPO) በማስያዝ መጫረት ይችላሉ።
3. ተጫራቾች የመረጡትን ሞተር ሳይከል/ሎች ለመግዛት የሚያቀርቡትን ዋጋ በታሸገ ኤንቨሎፕ በማድረግ እስከ ሐምሌ 20 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 11፡00 ድረስ በባንኩ ዋና መ/ቤት ህንጻ 12ኛ ፎቅ ለጨረታ በተዘጋጀው ሳጥን ማስገባት ይጠበቅባቸዋል፡፡
4. ጨረታው ሐምሌ 20 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 11፡00 ሰዓት ላይ ተዘግቶ ሐምሌ 21 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡30 ላይ በባንኩ ህንጻ 19ኛ ፎቅ በሚገኘው የስብሰባ አዳራሽ ይከፈታል፡፡
5. ጨረታው በሚካሄድበት ዕለትና ሰዓት መገኘት የሚችሉት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው ብቻ ናቸው።
6. አሸናፊው አሸናፊነቱ በደብዳቤ ከተገለጸለት ቀን ጀምሮ በ5 የስራ ቀናት ውስጥ ያሸነፈበትን ጠቅላላ ዋጋ ለባንኩ ከፍያ መፈጸም አለበት። ይህን ባያደርግ ግን ያስያዘው ሲፒኦ ለባንኩ ገቢ ሆኖ ጨረታው ይሰረዛል፤
7. ባንኩ ንብረቱን በገዢው ስም እንዲዞር ለሚመለከተው የመንግስት አካል ደብዳቤ ይጽፋል።
8. ከስም ዝውውር፤እንዲሁም ሞተሮቹን ከማስተካከል፤ከመጫንና ከማጓጓዝ ጋር የተያያዙ ማናቸውንም ከፍያዎች ገዢው ይከፍላል።
9. ተጨማሪ የጨረታ ደንቦች የጨረታ ሰነድና የዋጋ መሙያው ቅጽ ላይ ተቀምጠዋል፡፡
10. ባንኩ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
አድራሻ: - Sengatera, Ras. Abebe Aregay Street, P.O.Box 1212 Addis Ababa, Ethiopia
