Tender Detail

Tender Details


ሲንቄ ባንክ አ.ማ በአዋጅ ቁጥር 1147/2011 በተሰጠው ሥልጣን መሠረት ቀጥሎ የቀረበዉ ንብረት በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል:: 


                                             የሐራጅ ሽያጭ ማስታወቂያ

                                            ቁጥር ሲባ/ህአዲ/ሐራጅ/035/2018

የተበዳሪ ስም የንብረት አስያዥ ስም አበዳሪ ቅርንጫፍ ለጨረታ የቀረበው ንብረት መግለጫ የጨረታ መነሻ ዋጋ በብር

 

ጨረታው የሚከናወንበት ጨረታው የወጣው
      ቀን ሰዓት  
1

 

ጌትነት መገርሳ ጪብሳ ጌትነት መገርሳ ጪብሳ ኦዳ  ሱዙኪ እስዊፍት

ሞዴል 2022

AA-02-C29379 MBHCZC63S00B41169   1,824,000 24/11/2018 4፡30-5፡30 ለመጀመሪያ    ጊዜ

 

ሲንቄ ባንክ . በአዋጅ ቁጥር 1147/2011 በተሰጠው ሥልጣን መሠረት ቀጥሎ የቀረበዉ ንብረት በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል::                          

የሐራጁ ደንቦች፤  

  1. ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪል የጨረታውን መነሻ ዋጋ አንድ አራተኛ (1/4ኛ) በባንክ ክፍያ ማዘዣ (ሲ.ፒ.ኦ.) ብቻ በማስያዝ መጫረት ይችላሉ፡፡ አሸናፊ የሆነው ተጫራች ያሸነፈበትን ቀሪ ገንዘብ በአሥራ አምስት (15) ቀናት ውስጥ አጠቃሎ ካል ከፈለ ያስያዘው ገንዘብ ለባንኩ ገቢ ሆኖ ሐራጁ ይሰረዛል፡፡ በተጨማሪም ንብረቱ ድጋሚ ለሐራጅ ሲቀርብ ለሚታየው የዋጋ ልዩነት ይጠየቃል፡፡
  2. በሐራጁ ሂዳት ከፍተኛ ዋጋ ያቀረበው ተጫራች ማን እንደሆነ ብቻ የሚገለፅ ሲሆን ጨረታውን ያሸነፈው ሰው/አካል ስለማሸነፉ በሚመለከተው የባንኩ አካል ከተረጋገጠ በኃላ ማሸነፉን የሚገልጽ ደብዳቤ ይሰጠዋል::
  3. ላላሸነፉት ተጫራቾች ያስያዙት ሲ.ፒ.ኦ በዕለቱ ይመለስላቸዋል፡፡
  4. በሐራጅ ላይ መገኘት የሚችሉት ተጫራቾች፣ ተበዳሪ እና ንብረት አስያዥ ወይም ሕጋዊ ተወካዮች ብቻ ናቸው::
  5. ሐራጁ የሚካሄድበት ቦታ፤ ካዛንቺስ የምገኘዉ ሲንቄ ባንክ ዋና መስሪያ ቤት 7ኛ ፎቅ ይሆናል፡፡
  6. በጨረታዉ ቀን ከ4፡30 እስከ 5፡00 የተጨራቾች ምዝገባ ሰዓት ሲሆን፣ ከ5፡00 ሰዓት በኋላ የተጫራች ምዝገባ አይኖርም። ከ5፡00 – 5፡30 ሐራጁ የሚካሄድበት ጊዜ ይሆናል።
  7. ለስም ዝውውር የሚከፈል ክፍያ እንዲሁም የሊዝ እና ሌሎች ገዥ እንዲከፍላቸው በሕግ የተወሰኑ ከታክስ እና ግብር ጋር ተያያዥ የሆኑ ክፍያዎችን ገዢው/አሸናፊው ይከፍላል:
  8. የንግድ ማህበራትን በመወከል መጫረት የሚፈልግ ማንኛዉም ግለሰብ የማህበሩን ህጋዊ ሰዉነት ያለዉ መሆኑን የሚያረጋግጥ የመመስረቻ ወይም እና የመተዳደሪያ ደንብ እንዲሁም ህጋዊ የዉክልና ስልጣን ሰነድ ይዞ መቅረብ ይጠበቅበታል፡፡
  9. ባንኩ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
  10. ለሐራጅ የቀረበ ንብረትን ለመጎብኘት የሚፈልግ ከአበዳሪ ቅርንጫፍ ጋር አስቀድሞ ቀጠሮ በመያዝ መጎብኘት ይቻላል፡፡
  11. ተጫራች የጨረታ አሸናፊ ነዉ የሚባለዉ አሸናፊነቱን የሚገልፅ  ደብዳቤ በፅሑፍ ሲደርሰዉ ነዉ፡፡
  12. ለተጨማሪ መረጃ የሲንቄ ባንክ ህግ አገልግሎት ክፍል ስልክ ቁጥር (+251-11557-6016), ፤ ኦዳ ቅርንጫፍ (0115571965) ደውለው መጠየቅ ይችላሉ፡፡

ሲንቄ ባንክ አ.ማ                                       

Save Tender