የዲባዩ ክፍለ ከተማ ወረዳ ፍ/ቤት ፍ/ብሔር ችሎት:የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ማስታወቂያ
በፍ/ለሙበት፡- ዘነበ አለማየሁ እና በፍ/ባለዕዳ ብርሃኑ ጉተማ 1. በቢሾፍቱ ከተማ ዲባዩ ክፍለ ከተማ ቢፍቱ ወረዳ ውስጥ በ160 ካሬ ሜትር መሬት ላይ ሰፍሮ የሚገኝ መኖሪያ ቤት ካርታ ቁጥሩ Bl/17491/12 በሆነው በአፈፃፀም ተከሳሽ ባለቤት በወ/ሮ መሰረት እሸቱ ስም ተመዝግቦ የሚታወቅ ግምት ብር 1,715,091.38 (አንድ ሚሊዬን ሰባት መቶ አስራ አምስት ሺህ ዘጠና አንድ ብር ከሠላሳ ስምንት ሣንቲም) ነው፡፡ 2. የጨረታው ሽያጭ በግልጽ የሚሸጥ ሆኖ በዚህ iኛ ጨረታ ላይ ከተወዳዳሪዎች ውስጥ ከፍተኛ ዋጋ ላቀረበው የሚሸጥ ይሆናል፡፡ 3. ጨረታው የሚካሄድበት ቦታ ዲባዩ ክፍለ ከተማ ቢፍቱ ወረዳ በጨረታ የሚሸጥ መኖሪያ ቤት በሚገኝበት ቦታ ሆኖ ጠዋት ከ3፡00 ሰዓት ጀምሮ እስከ 6፡30 ሰዓት የሚካሄድ ይሆናል፡፡ 4. ጨረታውን ያሸነፈው ገዥ ከገዛበት ዋጋ ውስጥ ብር25% ወዲያው አስይዞ ቀሪውን ዋጋ በ10 ቀናት ውስጥ መክፈል አለበት፡፡ 5. ጨረታ ማስታወቂያ ለአንድ ወር ጊዜ ድረስ አየር ላይየሚቆይ ሆኖ የጨረታው ሽያጭ የሚካሄድበት ቀን 29/11/2018 ጠዋት ከ3፡00 ሰዓት እስከ 6፡30 ሰዓት መኖሪያ ቤቱ በሚሸጥበት ቦታ ይሆናል፡፡ 6. ማንኛውም የጨረታ ተወዳዳሪ ከጨረታው መነሻ ዋጋ ውስጥ 1/4ኛውን በCPO ማስያዝ አለበት፡፡7. የጨረታ ውጤት በ30/11/2018 ለከሰዓት በፊት ለ8፡00 ሰዓት እንደሚገልፅ ፍ/ቤቱ አዟል፡፡
የዲባዩ ክፍለ ከተማ ወረዳ ፍ/ቤት ፍ/ብሔር ችሎት
