ፀደይ ባንክ ለአቶ ወርቁ ሙኃባዉ ኃይሌ ለሰጠዉ ብድር በመያዣ የያዘዉን በአማራ ክልል ቡልጋ (ቱለፋ) ከተማ የሚገኘዉንና በአቶ አወቀ ዓለሙ ታዬ ስም የተመዘገበዉን የካርታ ቁጥር 704 የቦታዉ ስፋት 8990 ካ ሜ የሆነ የኢንዱስትሪ ሸድ እና ቦታ ለድርጅት አገልግሎት የሚዉል በአዋጅ ቁጥር 97/90 በተሰጠዉ ስልጣን መሰረት በግልፅ ጫረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡
ለሁለተኛ ጊዜ የወጣ የሐራጅ ሽያጭ ማስታወቂያ
ፀደይ ባንክ ለአቶ ወርቁ ሙኃባዉ ኃይሌ ለሰጠዉ ብድር በመያዣ የያዘዉን በአማራ ክልል ቡልጋ (ቱለፋ) ከተማ የሚገኘዉንና በአቶ አወቀ ዓለሙ ታዬ ስም የተመዘገበዉን የካርታ ቁጥር 704 የቦታዉ ስፋት 8990 ካ ሜ የሆነ የኢንዱስትሪ ሸድ እና ቦታ ለድርጅት አገልግሎት የሚዉል በአዋጅ ቁጥር 97/90 በተሰጠዉ ስልጣን መሰረት በግልፅ ጫረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡ በመሆኑም ተጫራቾች ለጫረታ ከመቅረባቸዉ በፊት የሚከተሉትን ደምቦች በመገንዘብና ቅድመ ሁኔታዎችን በማሟላት ተጫራቾች እንዲጫረቱ ይጋብዛል፡፡
- የቤቱ የጫረታ መነሻ ዋጋ ተጨማሪ እሴት ታክስን ሳይጨምር 42,034,860.14 (አርባ ሁለት ሚሊዮን ሰላሳ አራት ሺኅ ስምንት መቶ ስድሳ ብር ከአስራ አራት ሳንቲም) ብቻ
- ተጫራቾች የቤቱን ጨረታ መነሻ ዋጋ ብር ¼ (በጥሬ ገንዘብ ወይም በሲ.ፒ.ኦ) በጸደይ ባንክ አ.ማ ስም በማሰራት ለጫረታ ማስከበሪያ ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
- የጫረታዉ አሸናፊ አሸናፊነቱ የሚረጋገጠዉ የጫረታዉ ዉጤት በሚመለከተዉ አካል ጸድቆ በባንኩ ደብዳቤ ሲሰጠዉ ብቻ ይሆናል፡፡
- በጫረታዉ የሚሳተፈዉ በህግ ሰዉነት ያገኘ ከሆነ የድርጅቱ መመስረቻ ጽሁፍ ወይም መተዳደሪያ ደምብ፤ ህጋዊ ሰዉነት ያገኘበት የምዝገባ የምስክር ወረቀት እንዲሁም ህጋዊ ዉክልና ማቅረብ አለበት፡፡
- የጫረታዉ አሸናፊ አሸናፊነቱ በባንኩ በደብዳቤ ከተገለጸለት ቀን ጀምሮ ያሸነፈበትን ጠቅላላ ዋጋ በ10 ቀናት ዉስጥ አጠቃሎ መክፈልና በጫረታ ያሸነፈዉን ንብረት መረከብ ይኖርበታል፡፡ አሸናፊዉ በ10 ቀናት ዉስጥ ገንዘቡን ካልከፈለ ጨረታዉ ተሰርዞ ለጨራታ ማስከበሪያ ያስያዘዉ ገንዘብ ለባንኩ ገቢ ይሆናል፡፡
- በጫረታዉ ለተሸነፉ ተጫራቾች ያስያዙት ጥሬ ገንዘብ ወይም ሲ.ፒ.ኦ ይመለስላቸዋል፡፡
- የጫረታ አሸናፊዉ ከሚገዛዉ ንብረት ዋጋ በተጨማሪ ከቤቱ ጋር የተያያዙ ማናቸዉም ለመንግስት የሚከፈሉ ክፍያዎች፡ ግብር፤ ተጨማሪ እሴት ታክስ 15% እና ከስም ዝዉዉሩ ጋር የሚገናኙ ማንኛዉንም ወጭዎች ገዢ ይሸፍናል/ ይከፍላል/፡፡ ዉዝፍ የሊዝ ክፍያ ካለ ባንኩ የሚከፍል ሆኖ ለቀረዉና የክፍያ ጊዜዉ ላልደረሰ የሊዝ ክፍያ ገዢ ከሚመለከተዉ የመንግስት አካል ጋር በራሱ ዉል የሚወስድ ይሆናል፡፡
- ተጫራቾች ቤቱን /ድርጅቱን/ በባንኩ አማካኝነት መጎብኘት ወይም ማየት ይችላሉ፡፡
- ከፍ ሲል የተጠቀሰዉን ንብረት ለሚገዛና የባንኩን የብድር ፖሊሲና መመሪያ መመዘኛዎች ለሚያሟላና ፍላጎት ላለዉ ተጫራች በሚሰጠዉ ከፍተኛ ዋጋ ባንኩ እስከ 30% ( ሰላሳ በመቶ) ብድር ሊያመቻች ይችላል፡፡
- ጫረታዉ የሚካሄደዉ ነሃሴ 14/2018 ከጠዋቱ 3.00—5.00 የተጫራቾች ምዝገባ፤ ከ5.00 እስከ ቀኑ 6.00 ሰዓት ጫረታ በአዲስ አበባ ከተማ በልደታ ክ/ከተማ ልዩ ቦታዉ ሰንጋ ተራ በባንኩ ዋና መ/ቤት 11ኛ ፎቅ ይሆናል፡፡
- ባንኩ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጫረታዉን በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነዉ፡፡
- ለተጨማሪ መረጃ፡- ፀደይ ባንክ ዋና መ/ቤት በስ.ቁ +251115582978 ደዉሎ መጠየቅ ይቻላል፡፡
