የድል በትግል ቅድመ አንደኛ አንደኛ እና መካከለኛ ደረጃ ት/ቤት ለ2019 ዒ.ም በጀት ዓመት በውስጥ ገቢ በጀት ለት/ቤቱ አገልግሎት የሚውሉ ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን ስራዎች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል፡፡
የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታው ቁጥር 01/2019
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በጉለሌ ክ/ከተማ ት/ፅ/ቤት ወረዳ o1 ስር የሚገኘው የድል በትግል ቅድመ አንደኛ አንደኛ እና መካከለኛ ደረጃ ት/ቤት ለ2019 ዒ.ም በጀት ዓመት በውስጥ ገቢ በጀት ለት/ቤቱ አገልግሎት የሚውሉ ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን ስራዎች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል፡፡
ሎት 1፡- የአጥር ጥገና
ሎት 2፡- የመስኮት ጥገና
ሎት 3፡- የመምህራን ማረፊያ ሶፋ ጥገና
በዚህ ጨረታ ስመወዳደር የምትፈልጉና ከዚህ በታች የተጠቀሱትን መስፈርቶች የምታሟሱ
ህጋዊ ተወዳዳሪዎች፡-
1. በመንግስት ዕቃ አቅራቢነት ዝርዝር የተመዘገቡ የምስክር ወረቀት ያላቸው እና የቫት ተመዝጋቢ የሆኑ እና በዘመኑ የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያላቸው።
2. በጥቃቅን እና አነስተኛ በአምራችነት ተደራጅተው የሚመጡ ተወዳዳሪዎች በሚያቀርቡት የዋስትና ደብዳቤ መሰረት የሚስተናገዱ ይሆናል።
3. የእቃዎች ዋጋ 15% ቫት ተጨምሮ ይቅረብ፣ ባይቀርብ እንደተጨመረ ሆኖ የሚሰራ ይሆናል፡፡
4. ተጫራቾች የማይመለስ 200 (ሁለት መቶ ብር) በመክፈል የጨረታውን ዝርዝር መረጃ የያዘ ሰነድ ከት/ቤቱ ፋ/ግ/ን አስ/ደጋፊ የስራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 4 በመምጣት መውሰድ የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን።
5. ተጫራቾች የሚጫረቱበትን ዋጋ በገዙት ሰነድ ላይ ባለው የዋጋ ማቅረቢያ ቦታ በግልፅ መሙላት አለባቸው::
6. ተጫራቾች ለሎት1፡-15,000.00 ለሎት2:-15.000.00 ለሎት3:-15,000.00 የጨረታ ማስከበሪያ ብር በባንክ የተረጋገጠ ሲፒኦ ማስያዝ አለባቸው።
7. ተጫራቾች የተመረጡ እቃዎች እና ናሙና ጨረታው ከመከፈቱ በፊት ማቅረብ አለባቸው።
8. ተጫራቾች ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 10 (አስር) ተከታታይየስራ ቀናት ለዚሁ ጨረታ በተዘጋጀ ሳጥን በቢሮ ቁጥር 05 ማስገባት ይችላሉ፡፡
9. አሸናፊ ሆነው የተመረጡ ድርጅቶች የአሸነፉበትን ጠቅላላ ዋጋ 10% በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ የውል ማስከበሪያ ማቅረብ አለባቸው፡፡
10. አሸናፊው ተጫራች ያሸነፈባቸውን እቃዎች በራሳቸው የትራንስፖርት ወጭ ት/ቤቱ ንብረት ከፍል ድረስ ማምጣት አለባቸው፡፡ ት/ቤቱ ተጨማሪ የስራውን 20% የመጨመር ወይም የመቀነስ መብት አለው፡፡
11. ጨረታው ማስታወቂያው በወጣበት 10ኛው ቀን 11፡30 ሰዓት ላይ ተዘግቶ በ11ኛው ቀን ከጠዋቱ በ3፡30 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎች ቢገኙም ባይገኙም ቢሮ ቁጥር ዐ1 የሚከፈት ይሆናል፡፡
12. ት/ቤቱ የተሻለ መንገድ /አማራጭ/ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው::
አድራሻ፦ ጉለሌ ክ/ከተማ ሽሮሜዳ ከስፔን ኤምባሲ አጠገብ
ለበለጠ መረጃ ስልክ ቁጥር፡-om-54-20-95
የድል በትግስ ቅድመ አንደኛ አንደኛ እና መካከስኛ ደረጃ ት/ቤት
