Tender Detail

Tender Details

  • Company የከሚሴ ከተማ አስተዳደር ከተማ እና መሰረተ ልማት ጽ/ቤት
  • Address ከሚሴ ከተማ ፡ አማራ ክልል ፡ ኢትዯጵያ, Phone: 033 554 02-55
  • Website
  • Deadline29 Aug 2026, 10:00 AM
  • magazineAddis Zemen
  • Bid Document Priceየማይመለስ የኢትዮ. ብር 300/ሶስት መቶ ብር/
  • opening dateጨረታው 25/12/18 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡30 ሰዓት
  • Categories Building Materials

የግንባታ ማቴሪያል ግዥ - 10,000 ሊትር ሮቶ /ውሃ ማጠራቀሚያ/


የግንባታ ማቴሪያል ግዥ

የግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ

 

በአብክመ የከሚሴ ከተማ እና መሰረተ ልማት ጽ/ቤት በጽ/ቤቱ ሥር ለሚገኙ ለቄራ አገልግሎት ስራ ሱፐር ፋይበር 10,000 ሊትር ሮቶ /ውሃ ማጠራቀሚያ/እቃ ግዥ ለመፈፀም በዘርፉ የንግድ ፈቃድ ያላቸውን ድርጅቶች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።

ሎት ፡- 1 የግንባታ ማቴሪያል እቃ ግዥ

ስለሆነም በጨረታው ለመሳተፍ ፍቃደኛ የሆኑ: -

1.      ለስራው ህጋዊ ፈቃድ ኖሯቸው የዘመኑን ግብር የከፈሉና ያሳደሱ፤ ለስራው የምዝገባ የምስክር ወረቀት ያላቸው የቫት ተመዝጋቢ የሆኑና የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር/tin/ ያላቸው፣ ግዥው ከ200,000 ብር በላይ የሆነ የቫት ተመዝጋቢ የሆነ መሆን አለበት።

2.    የጨረታው ሰነድ ከከሚሴ ከተማ እና መሰረተ ልማት ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 33 በግዢ/ፋይ/ንብ/አስ/ዋና የስራ ሂደት ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ዕለት ጀምሮ ለ 15 /ለአስራ አምስት/ ተከታታይ ቀናት ከላይ የተዘረዘሩትን መረጃዎች ዋናና ኮፒ በመያዝ ዘወትር በስራ ቀንና ሰዓት ለእያንዳንዱ ሰነድ የማይመለስ የኢትዮ. ብር 300/ሶስት መቶ ብር/ በመክፈል የጨረታ ሰነዱን መውሰድ ይችላሉ።

3.    ተጫራቾች የጨረታውን ሰነድ ዋና እና ኮፒ በማድረግ በታሸገ ኤንቨሎፖች በአብክመ የከሚሴ ከተማ እና መሰረተ ልማት ጽ/ቤት በግዢ/ፋይ/ንብ/አስ/ዋና የስራ ሂደት ለዚሁ ተግባር በተዘጋጀው ሣጥን ውስጥ ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በአስራ ስድስተኛው /16/ቀን ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት እስከ 4፡00 ሰዓት ድረስ 10,000 ሊትር ሮቶ የውሃ ማጠራቀሚያ ግዥ ጨረታ ሰነድ ባለው ጊዜ ማስገባት ይኖርባቸዋል።

4.    ጨረታው 25/12/18 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡30 ሰዓት 10,000 ሊትር ሮቶ የውሃ ማጠራቀሚያ እቃዎች ግዥ ላይ በግዥ/ፋይ/ንብ/አስ/ዋና የስራ ሂደት ቢሮ ተጫራቾች ወይንም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል።

5.    ተጫራቾች ተመላሽ የሚደረግ የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ገንዘብ ሎት 1 -- 10,000 /አስር ሺህ ብር/

6.    የግንባታ ማቴሪያል እቃ ግዥ የጨረታ አሸናፊ የሆነው ድርጅት ውል በሚዋዋልበት ጊዜ የውለታ ማስከበሪያ ከአጠቃላይ ድምር ዋጋ 10% ማስያዝ ይኖርበታል።

7.    መሥሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉ ወይንም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።

8.    ተጨማሪ ማብራሪያ ከፈለጉ፤ በከሚሴ ከተማ እና መሰረተ ልማት ጽ/ቤት በግንባር በመቅረብ ወይንም በስልክ ቁጥር 033 554 0255 ደውለው መረዳት ይችላሉ።

 

በከሚሴ ከ/አስ/ የከተማና መሰረተ ልማት ጽ/ቤት

✨ messages.ai_summary
Procurement of a 10,000-liter water storage tank (roto) for construction material supply. Open tender for organizations with valid trade licenses, current tax clearance, VAT registration, and TIN. Bidders must submit bids with required documents and a refundable bid security.
Save Tender