የኤሌክትሪክ የእቃ ማጓጓዣ ጋሪ፣ የወረቀት መፍጫ ማሽን፣ የሽፍሻፊ ማሰሪያ ማሽን እና የኮምፒውተር እና ተዛማጅ እቃዎች ግዥ
የጨረታ ማስታወቂያ የጨረታ ቁጥር 022/18
ድርጅታችን ከዚህ በታች በሎት የተዘረዘሩትን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
- በጨረታ አንድ (ሎት 1) እስከ 1,500 ኪግ የመጫን አቅም ያለው በኤሌክትሪክ የሚሰራ የእቃ ማጓጓዣ ጋሪ (Electric Pallet Truck) ብዛት 2 ግዥ
- በጨረታ ሁለት (ሎት 2) የወረቀት መፍጫ ማሽን (Paper Shredder) ብዛት 1 ግዥ፤
- በጨረታ ሶስት (ሎት 3) ቁርጥራጭ ወረቀት/ሽፍሻፊ) ማሰሪያ ማሽን (Scrap paper Baler machine) ብዛት 1 ግዥ
- በጨረታ አራት (ሎት 4) - የኮምፒውተር እና ተዛማጅ እቃዎች ግዥ፤
| ተ.ቁ | አይነት | መለኪያ | ብዛት |
| 1 | Mac Computer | በቁጥር | 1 |
| 2 | Desktop Computer | በቁጥር | 7 |
| 3 | Printer | በቁጥር | 4 |
| 4 | Laptop | በቁጥር | 9 |
በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል። ስለሆነም ጠቅታዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸው የገንዘብ ሚኒስቴር የዕቃ አቅራቢዎች ምዝገባ የተጨማሪ እሴት ታክስ ምዝገባ የምስክር ወረቀት፣ የግብር ከፋይ ምስክር ወረቀት እና በጨረታ መሳተፍ የሚያስችል የታክስ ክሊራንስ ያላቸው ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን በድርጅቱ ዋና መ/ቤት (አራት ኪሎ) አዲሱ ህንፃ 1ኛ ፎቅ በሚገኘው የዕለት ገንዘብ ተቀባይ የማይመለስ ብር 300.00 ከፍለው በመግዛት የፋይናንሺያል እና የቴክኒካል የመጫረቻ ሰነዶቻቸውን ዋናውን እና ኮፒ በተለያየ ፖስታ በማድረግ በብርሃንና ሰላም ማተሚያ ድርጅት ነባሩ ህንፃ 6ኛ ፎቅ በሚገኘው ግዥና ንብረት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ቢሮ በተዘጋጀው ሣጥን ውስጥ ማስገባት ይችላሉ። ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ 30,000 (ሰላሳ ሺህ) ብር በባንክ ክፍያ ማዘዣ (ሲፒኦ) ማስያዝ አለባችሁ።
ጨረታው 3/13/8 ዓ.ም ከቀኑ 8:00 ሰዓት ተዘግቶ በዕለቱ የቴክኒካል መጫረቻ ሰነድ (ከላይ የተገለጸው ለቅደመ ግምገማ የሚያገለግሉ ዶክመንቶች፤ የጨረታ ማስከበሪያ) ብቻ ከሰዓት 8:30 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በብርሃንና ሰላም ማተሚያ ድርጅት ነባሩ ህንፃ 6ኛ ፎቅ በሚገኘው በግዥና ንብረት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ቢሮ ይከፈታል። የፋይናንሽያል የመጫረቻ ሠነዶች የሚከፈቱት ቴክኒካል ተቀባይነት ላገኙት ብቻ ነው። ድርጅቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ በጨረታው አይገደድም።
ስልክ ቁጥር 011-155-5230
ድረ ገፅ (www.ethbspe.org (https://www.ethbspe.org/))
አዲስ አበባ
ብርሃንና ሰላም ማተሚያ ድርጅት
Berhanena selam printing enterprise
