Tender Detail

Tender Details

  • Company በደቡብ ወሎ ዞን የአርጎባ ብሄረሰብ ልዩ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት
  • Address AMHARA Ethiopia, Phone: 0912716922
  • Website
  • Deadline10 Sep 2026, 10:00 AM
  • magazineAddis Zemen
  • Bid Document Priceብር 200 /ሁለት መቶ ብር/
  • opening dateበዚሁ ቀን ከረፋዱ 4:30 ይከፈታል
  • Categories Vehicle tire , Vehicle Spare Parts

በደቡብ ወሎ ዞን የአርጎባ ብሄረሰብ ልዩ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት አገልግሎት ለሚሰጣቸው የወረዳው ሴክተር መ/ቤቶች በ2019 በጀት አመት ለሴክተር መስሪያ ቤቶች የመኪና መለዋወጫ እቃዎችና የመኪና ጎማዎች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።


ሀገር አቀፍ ግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ

በደቡብ ወሎ ዞን የአርጎባ ብሄረሰብ ልዩ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት አገልግሎት ለሚሰጣቸው የወረዳው ሴክተር መ/ቤቶች በ2019 በጀት አመት ለሴክተር መስሪያ ቤቶች የመኪና መለዋወጫ እቃዎችና የመኪና ጎማዎች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል። በመሆኑም፤

  1. በዘመኑ የታደሰ ህጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸው፣
  2. የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር /Tin/ ያላቸው፣
  3. የግዥ መጠኑ 200,000.00 /ሁለት መቶ ሺህ ብር/ እና ከዚያ በላይ ከሆነ የተጨማሪ እሴት ታክስ /VAT/ የተመዘገቡ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፣
  4. ተጫራቾች በጨረታ ለመሣተፍ ከላይ ከተራ ቁጥር 1-3 የተጠቀሱትንና የሚመለከታቸው ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከመጫረቻ ሠነዶቻቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው።
  5. ተጫራቾች ኦሪጂናል ዕቃ መሙላት እና ያሸነፉባቸውን ዕቃ በባለሙያ ማስፈተሽ አለባቸው።
  6. የሚገዙ ዕቃዎችን ዓይነትና ዝርዝር መግለጫ /ስፔስፊኬሽን/ ከጨረታ ሠነዱ ማግኘት ይቻላል።
  7. ማንኛውም ተጫራች በሰነዱ ላይ ሲሞሉ ከእያንዳንዱ የዕቃ ዋጋ ላይ ቫትን ጨምሮ መሙላት አለባቸው፣
  8. ተጫራቾች የጨረታ ሠነዱን የማይመለስ ብር 200 /ሁለት መቶ ብር/ በመከፈል ከግዥ ንብረት አስተዳደር ቡድን ቢሮ ቁጥር 7 ማግኘት ይቻላል።
  9. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ለሚወዳደሩበት ብር የዕቃውን ጠቅላላ ዋጋ 15% በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ /C.P.O/ ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሠረተ የባንክ ዋስትና ወይም በጥሬ ገንዘብ ማስያዝ አለባቸው።
  10. ተጫራቾች በጥሬ ገንዘብ ሲያስይዙ በመምሪያው የገቢ ደረሰኝ ቆርጦ ኮፒውን ከኦሪጂናል ሰነዱ ጋር መታሸግ አለበት።
  11. አሸናፊው ተጫራች የአሸነፈበትን ጠቅላላ ዋጋ 10% የውል ማስከበሪያ የሚያስይዝ ይሆናል።
  12. ውድድሩ የሚካሄደው በጠቅላላ በሎት ድምር ነው።
  13. ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ሃሳቡን በአንድ ወይም አንድ ወጥ በሆነ ሁለት ቅጅዎች ማለትም ዋና እና ቅጅ በማለት በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ በአርጎባ ብሄረሰብ ልዩ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት በግዥ ንብ/አስ/ቡድን ቢሮ ቁጥር 7 ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ21 ተከታታይ ቀናት የጨረታ ሰነዱን መግዛትና በተዘጋጀው የጨረታ ሣጥን ውስጥ ማስገባት ይችላሉ።
  14. ጨረታው ተጫራቾች /ህጋዊ ወኪሎቻቸው/ በተገኙበት በግዥና ንብ/አስ/ቡድን ቢሮ ቁጥር 7 በ22ኛው ቀን ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ይታሸጋል። በዚሁ ቀን ከረፋዱ 4:30 ይከፈታል። የመከፈቻው ቀን የሥራ ቀን ካልሆነ በሚቀጥለው የስራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ከጠዋቱ 4:00 ሰዓት ታሽጎ 4፡30 ይከፈታል።
  15. በጨረታው ለመሣተፍ የሚፈልጉ ስለጨረታው ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ ቢሮ ቁጥር 7 ድረስ በአካል በመገኘት ወይም በስልክ ቁጥር 0912716922 በመደወል ማግኘት ይችላሉ።
  16. በመ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።

ማሳሰቢያ

አሸናፊው ድርጅት /ተጫራች/ ኦሪጅናል ዕቃ የማቅረብ ግዴታ አለባቸው እንዲሁም በየፑሉ በሚገኘው ንብረት ክፍል ገቢ ማድረግ ይኖርበታል።

በደቡብ ወሎ ዞን የአርጎባ ብሄረሰብ ልዩ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት

✨ messages.ai_summary
Procurement of vehicle spare parts and tires for sector offices in the Argoba special district, South Wollo Zone, via open national tender. Bidders need a valid trade license, TIN, and VAT registration if applicable. Winners must supply original goods and undergo inspection.
Save Tender