በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የኦሮሚያ ኢንቨስትመንት እና ኢንዱስትሪ ቢሮ በ2019 በጀት ዓመት የቢሮውን አገልግሎት ለማዘመን የሶፍትዌር ልማት (Software Development) ማሰራት ይፈልጋል።
የጨረታ ማስታወቂያ
በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የኦሮሚያ ኢንቨስትመንት እና ኢንዱስትሪ ቢሮ በ2019 በጀት ዓመት የቢሮውን አገልግሎት ለማዘመን የሶፍትዌር ልማት (Software Development / ለማሰራት ይፈልጋል በመሆኑም የሶፍትዌር አልሚ ድርጅቶች በጨረታ እንዲሳተፉ በጋዜጣ በማውጣት አጫርቶ ሶፍትዌር ማሰራት ይፈልጋል።
ስለዚህ የሚከተለውን የጨረታ መስፈርት የሚያሟሉ ተጫራቾች እንዲወዳደሩ ተጋብዘዋል።
1) ተጫራቾች በዘመኑ የታደሰ የንግድ ፍቃድ ያላቸውና የዘመኑ ግብር የከፈሉ እንዲሁም የተጨማሪ እሴት ታክስ / VAT /ተመዝጋቢ መሆን አለባቸው።
2) ተጫራቹ በባለፉት 3 (ሶስት) ተከታታይ ዓመታት በእያንዳንዱ ዓመት ቢያንስ 4,000,000 ብር የአመታዊ አማካይ ሽያጭ መጠን መኖር አለበት። ይህ ማለት በአጠቃላይ ቢያንስ 12,000,000 ብር የሶስት ዓመት ሽያጭ መኖር አለበት። ፍቃድ ባለው ኦዲተር የተረጋገጡ የፋይናንስ ሪፖርቶች መቅረብ አለባቸው።
3) ተጫራቹ ድርጅት በሶፍትዌር ልማት ዘርፍ ቢያንስ 6 (ስድስት) ዓመት እና ከዚያ በላይ ልምድ ያለው መሆን አለበት።
4) ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና አጠቃላይ የሚያቀርበትን የፋይናንስ ጥቅል ዋጋ 2% (ሁለት በመቶ) በባንክ በተመሰከረለት / CPO/ ማቅረብ አለባቸው።
5) ተጫራቾች ዝርዝር መግለጫ የያዘው የጨረታ ሰነድ ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ዘወትር በሥራ ሰዓት ወደ ቄራ በሚወስደው መንገድ ሣር ቤት የሚገኘው በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የኦሮሚያ ኢንቨስትመንት እና ኢንዱስትሪ ቢሮ 1ኛ ፎቅ በመቅረብ የማይመለስ ብር 1,000.00 /አንድ ሺህ ብር/ በመክፈል መግዛት ይችላሉ።
6) ተጫራቾች የጨረታውን ሰነድ ቴክኒካልና ፋይናንሻል ኦርጂናልና ኮፒውን በሁለት የተለያዩ ፓስታ በማሸግ ዘወትር በሥራ ሰዓት ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ10 ተከታታይ ቀናት ለዚሁ ጨረታ በተዘጋጀ የጨረታ ሣጥን ውስጥ እስከ 10ኛው ቀን 4፡30 ሰዓት ማስገባት ይኖርባቸዋል።
7) ይህ የጨረታ ማስታወቂያ በጋዜጣ አየር ላይ ከዋለበት ቀን ጀምሮ ለ10 ተከታታይ ቀናት ከቆየ በኋላ በ10ኛው ቀን ከጠዋቱ 4፡30 ታሽጎ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በኦሮሚያ ኢንቨስትመንት እና ኢንዱስትሪ ቢሮ 5፡00 ሰዓት ይከፈታል በዕለቱ በአል ወይም ዝግ ከሆነ በቀጣዩ የሥራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ጨረታው ይከፈታል።
8) ቢሮ የሚያሰራውን ሥራ 20% የመጨመርም ሆነ የመቀነስ መብቱ የተጠበቀ ነው።
9) ቢሮ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱየተጠበቀ ነው።
ማሳሰቢያ፦ ተጫራቾች ሥራውን በተባለው ጊዜ ውስጥ አጠናቀው ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
አድራሻ : በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ሣር ቤት
በሚገኘው ህንፃ 1ኛ ፎቅ
የኦሮሚያ ኢንቨስትመንት እና ኢንዱስትሪ ቢሮ ነው
ለተጨማሪ ማብሪሪያ
በስልክ ቁጥር 0911631348/0913152039/0917805333 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ።
በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የኦሮሚያ ኢንቭስትመንት እና ኢንዱስትሪ ቢሮ
