በአምቦ ሪጅን ስር በተለያዩ ቦታዎች- አምቦ፤ ወሊሶ፣ ቱሉ ቦሎ፤ ሰደን ሶዶ፤ ባኮ፤ እና ጌዶ ተከማችተው የሚገኙ ተቀቅለው ያገለገሉ የእንጨት ምሶሶዎችን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል።
ያለገሉ እቃዎች ሽያጭ ግልጽ ጨረታማስታወቂያ
ጨረታ ቁጥር ኢ/ኤ/አ/ሪ/ግ/ጨ/001/2019
በአምቦ ሪጅን ስር በተለያዩ ቦታዎች- አምቦ፤ ወሊሶ፣ ቱሉ ቦሎ፤ ሰደን ሶዶ፤ ባኮ፤ እና ጌዶ ተከማችተው የሚገኙ ተቀቅለው ያገለገሉ የእንጨት ምሶሶዎችን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል።
|
ተ.ቁ
|
የእቃው ዓይነት
|
የጨረታ መዝጊያ ቀን እና ሰዓት
|
የጨረታ መክፈቻ ቀን እና ሰዓት
|
የጨረታ ዋስትና ማስከበሪያ
|
|
1
|
ተቀቅለው ያገለገሉ የእንጨት ምሶሶዎችን
|
ጳጉሜ 04 ቀን 2018 ዓ.ም 8፡00 ሰዓት
|
ጳጉሜ 04 ቀን 2018 ዓ.ም 8፡30 ሰዓት
|
ብር 25,000.00 (ሃያ አምስት ሺ ብር)
|
1. ማንኛውም የንግድ ፈቃድ ያለው፣ የትኛውም አካል እና ማንኛውም የንግድ ፍቃድ የሌለው ግለሰብ የጨረታ ሰነድ ገዝቶ የጨረታ ዋስትና በማስያዝ በጨረታው መሳተፍ ይችላሉ።
2. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ማስታወቂያው በጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ የማይመለስ ብር 600.00 (ስድስት መቶ ብር) በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አካውንት ቁጥር (1000254843017 EEU Ambo District Connection Fee) በሚለው ገቢ በማድረግ እና የከፈሉበትን የባንክ ስሊፕ ይዞ በመምጣት መውሰድ ይችላሉ።
3. አድራሻ፡- አምቦ ከተማ ቀበሌ 01 የቤት ቁጥር-- የድሮ ሃዮሜ ኮሌጅ ሕንፃ ላይ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አምቦ ሪጅን የአቅርቦት ሰንሰለት እና ንብረትና ጠቅላላ አገልግሎት 2ተኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 14
4. ተጫራቾች ለጨረታ ዋስትና ማስከበሪያ የሚያቀርቡት የገንዘብ መጠን ከላይ በሠንጠረዡ ውስጥ በተገለፀው መሠረት ሆኖ በባንክ በተረጋገጠ ቼክ /CPO/ ወይም በቅድመ ሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና (Bid Bond) ማስያዝ ይኖርባቸዋል።
5. ተጫራቾች የመወዳደሪያ ሰነዳቸውን በታሸገ ኤንቬሎፕ በማድረግ ጨረታ ቁጥር፡ ኢ/ኤ/አ/አ/ሪ/ግ/ጨ/001/2019 የሚል ምልክት በማድረግ እስከ ጳጉሜን 4 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ድረስ ከላይ በተጠቀሰው አድራሻ ለዚሁ ጨረታ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት የሚኖርባቸው ሲሆን ጨረታው በተመሳሳይ ቀን ከቀኑ 8፡30 ሰዓት የሚከፈት ይሆናል፣
6. ጨረታው ከላይ በተገለፀው መሠረት ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፣
7. ተጫራቾች ተጨማሪ ማብራሪያ ከፈለጉ በስልክ ቁጥር +251-112-609777 መደወል ይችላሉ።
8. ድርጅቱ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ማሳሰቢያ፡- የእንጨት ምሶሶዎችን በተመለከተ ፈፅሞ ለማገዶነት (ለምግብ ማብሰያነት) እና ለኤሌክትሪክ መስመር ዝርጋታ የማያገለግሉ ሲሆን ለመግዛት የሚቀርቡ ድርጅቶች ወይም ግለሰቦች ግዥውን ፈፅመው ከወሰዱ በኋላ በሰው፣ በእንሰሳት እና በተፈጥሮ (አካባቢ) ላይ ጉዳት በማያደርስ መልኩ በኃላፊነት መልሰው በሥራ ላይ የሚያውሉ መሆንና በዚሁ አግባብም እንደሚጠቀሙ በደብዳቤ ማሳወቅ ይኖርባቸዋል።
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አምቦ ሪጅን
