የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮ የተለያዩ የህትመት ስራዎች፣ የአገልግሎት ኪራይ፣ የመኪና ጌጣጌጥ፣ የተለያዩ ኤሌክትሮኒክስ ጥገና፣ ካሜራ ከነሙሉ አክሰሰሪው እና የተለያዩ የኤሌክትሮኒክስ ግዥ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ግዥ መፈጸም ይፈልጋል
የጨረታ ማስታወቂያ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮ ለ2017 በጀት ዓመት ከሎት 1-6 ድረስ ለአንድ አመት የሚቆይ ውል በመግባት በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ግዥ መፈፀም ይፈልጋል ።
በዚሁ መሰረት፡-
- ሎት1- የተለያዩ የህትመት ስራዎች፣
- ሎት 2 - የአገልግሎት ኪራይ፣
- ሎት 3 - የመኪና ጌጣጌጥ፣
- ሎት 4 - የተለያዩ ኤሌክትሮኒክስ ጥገና፣
- ሎት 5 - ካሜራ ከነሙሉ አክሰሰሪው፣
- ሎት 6 - የተለያዩ የኤሌክትሮኒክስ ግዥ፣
- በዘርፉ ህጋዊ ፈቃድ ያለውና የ2016 የታደሰ የንግድ ስራ ፍቃድ ያላቸው፡፡
- የጨረታ ማስከበሪያ ብር 50,000 (ሃምሳ ሺህ ብር) ወይም በባንክ የተረጋገጠ የክፍያ ማዘዣ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮ ስም CPO ጋራንቲ (ቢድ ቦንድ) በማሰራት ማስያዝ የሚችሉ፡፡
- የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትናው ፀንቶ የሚቆይበት ጊዜ ከመጨረሻው ቀን በኋላ ለተጨማሪ 28 ቀናት ፀንቶ ይቆያል፡፡
- ይህ የጨረታ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15ተከታታይ የስራ ቀናት የማይመለስ 500 /አምስት መቶ ብር/ በመክፈል የጨረታ ሰነዱን መግዛት ይችላሉ፡፡
- ማንኛውም ተጫራች በዘርፉ የመልካም ስራ አፈጻፀም ወይም የምስክር ወረቀት ማስረጃ ማቅረብ የሚችል።
- የጨረታ ማስታወቂያው ከወጣበት ከመጀመሪያው ቀን ጀምሮ በ15 ተከታታይ የስራ ቀናት ከሰኞ እስከ አርብ ከ2፡30 – 11፡00 ሰዓት ድረስ የግዥ ዳይሬከቶሬት ቢሮ ቁጥር 803 ለዚሁ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
- የጨረታ ማስታወቂያው በወጣ በ16ኛ ቀን ማለትም የስራ ቀን ካልሆነ ቀጥሎ ባለው የስራ ቀን ከጠዋቱ 4:00 ሰዓት ታሽጎ በዚያኑ ቀን ከጠዋቱ 4፡30 ሰዓት ላይ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡ ነገር ግን ጨረታው በሚከፈትበት ቀን ተወዳዳሪዎች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው ባለመገኘታቸው ምክኒያት ጨረታውን ከመከፈት አያስቀርም፡፡
- ማንኛውም ተጫራች በሌሎች ተጫራቾች ላይ ተንተርሶ ዋጋ መስጠት (ማቅረብ) አይቻልም፡፡
- ቢሮው የገበያ ማዕከላቱ አይነት እና ብዛቱን በተመሰከተ በጨረታ ሰነዱ ላይ በገለፅነው መሰረት መቀነስና መጨመር የሚችል መሆኑን እንገልጻለን፡፡
- የጨረታው አሸናፊ ድርጅት ወይም ግስሰብ ማሸነፉ በቢሮው ከተገለጸበት ቀን ጀምሮ ቢበዛ በ20 ተከታታይ የሥራ ቀናት ውስጥ ከቢሮው ጋር ውል መግባት የሚችል፡፡
- ቴክኒካል አንድ ኦሪጅናል እና አንድ ኮፒ እንዲሁም ፋይናንሽያል አንድ ኦሪጂናል እና አንድ ኮፒ በማለት በሰም በታሸገ ፖስታ የድርጅቱ ስራ አስኪያጅ ስም፣ ፊርማ፣ የድርጅቱ ማህተም እና የድርጅቱ አድራሻ በመግለጽ ማስገባት ይኖርበታል፡፡
- ቢሮ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይንም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ለተጨማሪ ማብራሪያ በስልክ ቁጥር፡- 011-8-12-61-79/011-1-70-30-24 በመደወል መረጃ መጠየቅ ይቻላል።
አድራሻ፡- በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮ ደጃች ውቤ 1888 ህንጻ 8ኛ ፎቅ የቢሮ ቁጥር 803
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮ
