ኢትዮጵያን ሴንተር ፎር ዴቨሎፕመንት ሀገር በቀል የሆነና ለትርፍ ያልተቋቋመ የልማት ድርጅት ሲሆን ላለፉት ዓመታት ውጤታማ የሆኑ ፕሮጄከቶችን በመንደፍ ከተለያዩ ለጋሽ ተቋማት በሚያገኘው የገንዘብ ድጋፍ የተለያዩ የማህረሰብ ክፍሎችን በተለይም ሴቶችን ወጣቶችንና ታዳጊዎችን ተጠቃሚ ሲያደርግ የቆየ ሲሆን፤ ከጁላይ 1/2022 ጀምሮ ተግባራዊ መደረግ የጀመረ በተለይም በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ የሚኖሩ ስደተኞችን እና ወጣት ዜጎች ላይ ትኩረቱን ያደረገ ፕሮጀክት ከፕላን ኢንተርናሽናል ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር ከፕላን ዴንማርክ ባገኘው የገንዘብ ድጋፍ እየተገበረ ይገኛል፡፡ ለዚህ ፕሮጀክት ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን ቁሳቁሶች አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
የጨረታ ማስታወቂያ
ኢትዮጵያን ሴንተር ፎር ዴቨሎፕመንት ሀገር በቀል የሆነና ለትርፍ ያልተቋቋመ የልማት ድርጅት ሲሆን ላለፉት ዓመታት ውጤታማ የሆኑ ፕሮጄከቶችን በመንደፍ ከተለያዩ ለጋሽ ተቋማት በሚያገኘው የገንዘብ ድጋፍ የተለያዩ የማህረሰብ ክፍሎችን በተለይም ሴቶችን ወጣቶችንና ታዳጊዎችን ተጠቃሚ ሲያደርግ የቆየ ሲሆን፤ ከጁላይ 1/2022 ጀምሮ ተግባራዊ መደረግ የጀመረ በተለይም በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ የሚኖሩ ስደተኞችን እና ወጣት ዜጎች ላይ ትኩረቱን ያደረገ ፕሮጀክት ከፕላን ኢንተርናሽናል ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር ከፕላን ዴንማርክ ባገኘው የገንዘብ ድጋፍ እየተገበረ ይገኛል፡፡ ለዚህ ፕሮጀክት ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን ቁሳቁሶች አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
የጋርመንት ማስተማሪያ ቁሳቁሶች (ሎት 1)
የሆቴል ኦፕሬሽን ማስተማሪያ ቁሳቁሶች (ሎት 2)
የተለያዩ የፅዳት ቁሳቁሶች (ሎት 3)
በመሆኑም በዘርፉ የተሰማራችሁ እና ቀጥሎ የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የምታሟሉ ድርጅቶች በጨረታው መሳተፍ የምትችሉ መሆኑን እየገለጽን፤ መሟላት ያለባቸው መስፈርቶችም፡-
- በዘርፉ የተሰማሩ መሆኑን የሚገልጽ ለዘመኑ የታደሰ የንግድ ፍቃድ ማቅረብ የሚችሉ፣
- ቲን ነምበር ሰርተፊኬት ማቅረብ የሚችሉ፣
- የቫት /ቲኦቲ ተመዝጋቢ የሆኑ፣ እንዲሁም
- ቁሳቁሶቹን በተቀመጠው ስፔሲፊኬሽን መሠረት ማቅረብ የሚችሉ የእቃዎቹን ጥራት ሳምፕል አቅርበው ማሳየት የሚችሉ እና ለእቃዎቹ ጥራት ዋስትና መስጠት የሚችሉ፣
- ያሸነፉበትን እቃዎች በራሳቸው ትራንስፖርት አጓጉዘው ድርጅቱ ወደሚያዘጋጀው ስቶር ማድረስ የሚችሉ፣
ከላይ የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የምታሟሉ ተጫራቾች ይህ የጨረታ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ዕለት አንስቶ ለ7 (ሰባት) ተከታታይ የሥራ ቀናት ኢትዮጵያን ሴንተር ፎር ዴቬሎፕመንት /ECD/ ቢሮ በመምጣት የጨረታውን ሰነድ በነጻ በመውሰድ ቁሳቁሶቹን የምታቀርቡበትን ዋጋ በመሙላት በታሸገ ኤንቨሎፕ ገቢ አድርጋችሁ እንድትወዳደሩ እንገልፃለን፡፡
አድራሻ፦ ቦሌ አለም ህንፃ 7ኛ ፎቅ
ስልክ ቁጥር :- 011 663 95 16/17
ማሳሰቢያ፡- ድርጅታችን ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ
ኢትዮጵያን ሴንተር ፎር ዲቨሎፕመንት /ECD/
