በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የጎንደር መንገድ ጥገና ዲስትሪክት አይነታቸው የተለያየ 11,120 በርሜል አስፋልት (ሬንጅ) ከአዲስ አበባ- አዘዞ (ጎንደር) ማጓጓዝ ይፈልጋል፡፡
የጨረታ ማስታወቂያ
የግዥ መለያ ቁጥር GN- 007/2017
በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የጎንደር መንገድ ጥገና ዲስትሪክት አይነታቸው የተለያየ 11,120 በርሜል አስፋልት (ሬንጅ) ከአዲስ አበባ- አዘዞ (ጎንደር) ማጓጓዝ ይፈልጋል፡፡
ስለሆነም በጭነት ማጓጓዝ ዘርፍ ሕጋዊ ፈቃድ ያላቸው እና ለሥራው ብቁ የሆኑ ድርጅቶች በጨረታው መሳተፍ የሚችሉ ሲሆን፣ የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 500 በመከፈል በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ዋናው መ/ቤት የዕቃ ግዥ ዳይሬክቶሬት ወይንም ጎንደር ከተማ ቀበሌ 15 ከሚገኘው የዲስትሪከቱ ጽ/ቤት መውሰድ ይችላሉ፡፡
ተጫራቾች የዘመኑን ግብር የከፈሉና የታከስ ክሊራንስ ያላቸው፣ በመንግስት ዕቃ ግዥ የአቅራቢዎች ዝርዝር የተመዘገቡ፣ በተጨማሪ እሴት ታክስ ከፋይነት የተመዘገቡ እና በትራንስፖርት ባለስልጣን ያስመዘገቧቸው ቢያንስ 10 የሚሆኑ የራሳቸው የጭነት ተሽከርካሪዎች ከነተሳቢያቸው ያላቸው መሆኑን የሚያሳይ የምዝገባ ሰርተፍኬት ማቅረብ የሚችሉ መሆን ይጠበቅባቸዋል፡፡
መ/ቤቱ በማንኛውም ሁኔታ ጨረታውን የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ለተጨማሪ መረጃ ስልክ ቁጥር፡- 0911-664988 / 0925-356890
በመደወል ማግኘት ይቻላል።
የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ጎንደር መንገድ ጥገና ዲስትሪክት
