ሞሃ የለስላሳ መጠጦች ኢንዱስትሪ አክሲዮን ማህበር ሽሮ ሜዳ በሚገኘው የድርጅቱ መጋዘን ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን የተለያዩ ዓይነት ያገለገሉ ዕቃዎች በጨረታ በማወዳደር ባሉበት ሁኔታ መሸጥ ይፈልጋል፡፡
ያገለገሉ ዕቃዎች የጨረታ ሠነድ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር - Service 0008/2017
ሞሃ የለስላሳ መጠጦች ኢንዱስትሪ አክሲዮን ማህበር ሽሮ ሜዳ በሚገኘው የድርጅቱ መጋዘን ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን የተለያዩ ዓይነት ያገለገሉ ዕቃዎች በጨረታ በማወዳደር ባሉበት ሁኔታ መሸጥ ይፈልጋል፡፡ ስለዚህ ዕቃዎቹን መግዛት የሚፈልግ ማንኛውም ተጫራች የማይመለስ ብር 200.00 (ሁለት መቶ ብር) በመክፈል ለዚሁ የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ሸገር ዱቄትና ዳቦ ፋብሪካ ቅጥር ግቢ አዲስ በተገነባው ህንጻ ሦስተኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 003 በመውሰድ በጨረታው መሳተፍ ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች ለጨረታ የቀረቡትን የተለያዩ ዓይነት ያገለገሉ ዕቃዎችን ሽሮሜዳ በሚገኘው የድርጅቱ መጋዘን በአካል ተገኝተው በማየት ዋጋቸውን በታሸገ ኤንቬሎፕ ከታህሣሥ ቀን 2017 ጀምሮ ለተከታታይ 5 የሥራ ቀናት ከቀኑ 8:00 ሰዓት ድረስ ከላይ በተገለጸው መ/ቤት አድራሻ ለዚሁ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይችላሉ::
- ጨረታው በተመሳሳይ ቀን ከቀኑ 8፡00 ላይ ተዘግቶ 8፡30 ሰዓት ላይ በዋናው መ/ቤት መገኘት በሚፈልጉ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው ፊት ይከፈታል::
- በጨረታው የሚሳተፍ ድርጅት 20,000.00 (ሃያ ሺህ ብር) የጨረታ ማስከበሪያ CPO ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
- መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
አድራሻ፣
አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ሸገር ዱቄትና ዳቦ ፋብሪካ ቅጥር ግቢ አዲስ በተገነባው ህንጻ ሶስተኛ ፎቅ
ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ከታህሳስ 5 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ታህሳስ 11 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 8:00 ሰዓት ድረስ የጨረታ ሰነዱን በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ በማሸግና የጨረታ ሳጥን ውስጥ በማስገባት መወዳደር ይችላሉ፡፡
ማሳሰቢያ ፡- ሲፒኦውን በማንኛውም ባንክ በሞሃ የለስላሳ መጠጦች ኢንዱስትሪ አክሲዮን ማህበር ስም ማሰራት ይችላሉ፡፡
ሞሃ የለስላሳ መጠጦች ኢንዱስትሪ አክሲዮን ማህበር
