የአዳማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት በፍርድ ባለ መብት ህዳሴ ቴሌኮም አ.ማ ደቡብ ምስራቅ ዲስትሪክት እና በፍርድ ባለመ እዳ ወ/ሮ አይናለም አየለ መካከል ያለውን የፍርድ አፈጻጸም ክርክርን በተመለከተ የፍርድ ባለ እዳ ንብረት የሆኑት አክስዮኖች በጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል።
ለ2ኛ ጊዜ የወጣ ጨረታ ማስታወቂያ
በፍርድ ባለ መብት ህዳሴ ቴሌኮም አ.ማ ደቡብ ምስራቅ ዲስትሪክት እና በፍርድ ባለመ እዳ ወ/ሮ አይናለም አየለ መካከል ያለውን የፍርድ አፈጻጸም ክርክርን በተመለከተ የፍርድ ባለ እዳ ንብረት የሆኑት 2347.0152 (ሁለት ሺህ ሶስት መቶ አርባ ሰባት ነጥብ ዜሮ አንድ አምስት ሁለት) አክሲዮኖች በፍርድ ባለ እዳ ስም ተመዝግቦ የሚገኝ ስለሆነ የአንድ አክሲዮን ዋጋ ብር 100 (አንድ መቶ) ሲሆን 2347.0152 (ሁለት ሺህ ሶስት መቶ አርባ ሰባት ነጥብ ዜሮ አንድ አምስት ሁለት) አክሲዮኖች ብር 234,701.52 (ሁለት መቶ ሰላሳ አራት ሺህ ሰባት መቶ አንድ ብር ከ52 ሣን) በግልጽ ጨረታ በህዳሴ ቴሌኮም አ.ማ አዲስ አበባ ዋና መ/ቤት ጊቢ ውስጥ በ09/04/2017 ከ3:00 - 6፡00 ሰዓት በተቋቋመ የጨረታ ኮሚቴ የሚሸጥ ስለሆነ መግዛት የምትፈልጉ ግለሰቦች /ድርጅቶች / ቀርባችሁ ተጫርታችሁ መግዛት የምትችሉ መሆኑን የአዳማ ከተማ ከፍተኛ ፍ/ቤት ያሳውቃል፡፡
መግዛት የሚፈልግ ግለሰብ ወይንም ድርጅት ግምት ዋጋ 234,701.52 (ሁለት መቶ ሰላሳ አራት ሺህ ሰባት መቶ አንድ ብር ከ52 ሣን.) 1/4 በሲፒኦ ሲንቄ ባንከ ገቢ ማድረጉን ማስረጃ ማቅረብ አለበት፡፡
የአዳማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት
