የአባይ ጥጥ መዳመጫ ኃ.የተ.የግ.ማህበር ባለአክሲዮኖች በኩባንያው ውስጥ ያላቸውን አክሲዮን በዚህ የጨረታ ሰነድ የተዘረዘሩትን መስፈርቶች አሟልቶ አክሲዮን ለሚገዛ ማንኛውም ተጫራች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል::
የጨረታ ማስታወቂያ
የባለአክሲዮኖች የአክሲዮን ዕጣ ሽያጭ
የአባይ ጥጥ መዳመጫ ኃ.የተ.የግ.ማህበር ባለአክሲዮኖች በኩባንያው ውስጥ ያላቸውን አክሲዮን በዚህ የጨረታ ሰነድ የተዘረዘሩትን መስፈርቶች አሟልቶ አክሲዮን ለሚገዛ ማንኛውም ተጫራች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል::
- የጨረታ ሰነድ ሽያጭ የሚከናወነው በአዲስ አበባ ወሎ ሰፈር አምባሰል ሕንፃ በሚገኘው ሁለተኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 5 ንጋት ኮርፖሬት አዲስ አበባ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ወይም ባሕር ዳር ንጋት ኮርፖሬት ዋናው መ/ቤት ቀበሌ 16 አምባሰል ሕንፃ ጀርባ ንጋት ኮርፖሬት በሚገኘው ቢሮ ቁጥር 03 ሲሆን ይህ ማስታወቂያ ከተገለጸበት/ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ30 ተከታታይ ቀናት በሥራ ሰዓት የማይመለስ ብር 200.00 /ሁለት መቶ ብር/ ከፍሎ መውሰድ ይቻላል፡፡
- የማኅበሩን ባለአክሲዮኖች አክሲዮን ለመግዛት ፋብሪካውን ማየት ለሚፈልጉ ተጫራቾች የአባይ ጥጥ ማዳመጫ ኃ.የተ.የግ.ማህበር በአማራ ክልል፤ አዊ ብሄረሰብ አስተዳደር ዞን፤ በቻግኒ ከተማ አስተዳደር ከተማ በ02 ቀበሌ ይገኛል፡፡
- ኩባንያው በዋናነት መሠረታዊ የሚባሉ መሠረተ ልማቶች (መንገድ፣ መብራት፣ ውሃ እና ስልክ) የተሟሉለት ሲሆን ማስታወቂያው ከወጣበት ቀን ጀምሮ በተከታታይ እስከ 20 ቀናት ባለው ጊዜ ውስጥ በኩባንያው ቅጥር ግቢ ውስጥ በአካል በመገኘት መጎብኘት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች መግዛት የሚፈልጉትን አክሲዮን ከጨረታ ሰነዱ ጋር ተያይዞ በሚገኘው የዋጋ ማቅረቢያ ሠንጠረዥ የሚጫረቱበትን ዋጋ በመሙላት በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ ጨረታው በጋዜጣ (በማስታወቂያ) ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 31 ቀን ከጧቱ 4፡00 ሰዓት ድረስ በአዲስ አበባ ከተማ ወሎ ሰፈር አምባሰል ሕንጻ በሚገኘው ንጋት ኮርፖሬት አዲስ አበባ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ሁለተኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 5 ለዚሁ ተግባር በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይችላሉ፡፡
- የጨረታ ማስታወቂያው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 30 ተከታታይ ቀናት አየር ላይ የሚቆይ ሲሆን በ31ኛው ቀን ጧት 4፡00 የጨረታ ሳጥኑ ታሽጎ በዚሁ ቀን ከጠዋቱ 4፡30 ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በአዲስ አበባ ከተማ ወሎ ሰፈር አምባሰል ሕንጻ ሁለተኛ ፎቅ በሚገኘው ንጋት ኮርፖሬት አዲስ አበባ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 5 የሚከፈት ሲሆን የተጫራቾች አለመገኘት የጨረታውን መከፈት አያግደውም፡፡
- ተጫራቾች የአክሲዮኖችን ዕጣ ለመግዛት የሞሉትን ዋጋ 2% (ሁለት በመቶ) የሚሆን ገንዘብ የጨረታ ማስከበሪያ ቢድ ቦንድ በባንክ የተረጋገጠ በሁኔታ ላይ ያልተመሠረተ የጨረታ ማስከበሪያ ሲፒኦ ከባለአክሲዮኖች በአንዱ ማለትም በንጋት ኮርፖሬት ስም በማሠራት ኦርጂናሉን ከጨረታ ፖስታው ውስጥ አስገብተው ከሞሉት ዋጋ ጋር ማቅረብ ወይም በጥሬ ገንዘብ ማስያዝ አለባቸው፡፡
- ባለአክሲዮኖች በጨረታው ላይ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብታቸው የተጠበቀ ነው፡፡
- ባለአክሲዮን ማለት በኩባንያው ውስጥ የአክሲዮን ባለቤት የሆኑትን ንጋት የዘለቄታ የበጎ አድራጎት ድርጅት፣ አምባሰል የንግድ ሥራዎች ኃ/የተ/የግ/ማኅበር እና ጥቁር ዓባይ ትራንስፖርት ድርጅት ማለት ነው።
- ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር 0912028400 ወይም 0912960687 ወይም 0933634958 ደውሎ መጠየቅ ይቻላል፡፡
የአባይ ጥጥ መዳመጫ ኃ.የተ.የግ.ማህበር
