Tender Detail

Tender Details

  • Company Dilla Polytechnic College (ዲላ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ)
  • Address ዲላ ከተማ ፡ ደቡብ ክልል ፡ ኢትዮጵያ, Phone: 0463312719
  • Website
  • Deadline27 Dec 2024, 9:30 AM
  • magazine
  • Bid Document Price
  • opening date
  • Categories Educational And Training Equipment And Machinery

የዲላ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በ2017 ዓ/ም የበጀት ዘመን ለትምህርት ስልጠና የሚውሉ ዕቃዎችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል። 


የዕቃ  ግዥ  የጨረታ  ማስታወቂያ

 

የዲላ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ 2017 / የበጀት ዘመን ለትምህርት ስልጠና የሚውሉ ዕቃዎችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል። 

በመሆኑም ዕቃዎች የሚገዛላቸው የትምህርት ክፍሎች

1. ኮንስትራክሽን /       2. ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ /     3. አርባን ግርነር /

4. ብዩልዲንግ ኤሌክትሪካል ኢንስታሌሽን /     5. አግሮ ፕሮሰሲንግ /

6. ሳንተሪ ኢንስታሌሽን /     7. የእንጨት ሥራ /     8. ጋርመንት /

9. አኒማል ፕሮዳክሽን     10. የሥልጠና /መሳሪያዎች እና የጽዳት ዕቃዎች

11. የቆዳና የቆዳ ውጤቶች /     12. ማኒፋክቸሪንግ /

13. ኤሌክትሪካል ኤሌክትሮኒክስ /    14. አውቶ መካኒክስ /    15. ሮድ ኮንስትራክሽን /

16. ሆቴል /     17. ፕላፕንግ ዲፖርትመንት     18.  ሞተር ሳይክሎች

በመሆኑም ከላይ ለተዘረዘሩ የሥልጠና ዘርፎች ለመወዳደር የምትፈልጉ ተወዳዳሪዎች አቅራቢዎች ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን ማሟላት ይጠበቅባቸዋል።

  1. ጨረታውን ተወዳድሮ /አቅራቢ ድርጅት 2017 / የታደሰ የንግድ ፍቃድ ማቅረብ የሚችል መሆን ይጠበቅበታል።
  2. የገንዘብና ኢኮ//ሚኒስቴር ባዘጋጀው የዕቃ አቅራቢዎች ዝርዝር ውስጥ የተመዘገቡ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ ማስረጃ ማቅረብ አለባቸው።
  3. ተጫራቾች የተጨማሪ እሴት ታክስ ቫት ተመዝጋቢ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ ማስረጃ ማቅረብ አለባቸው።
  4. ተጫራቾች የተዘረዘሩትን ዕቃዎች ናሙና ማቅረብ የሚችሉና ቋሚ ዕቃዎችን ገዥው /ቤት በአካል ቀርቦ ለማየት ከፈለገ ለመተባበር ፍቃደኛ ሊሆኑ የሚችሉ መሆን አለባቸው።
  5. ተጫራቾች የዋጋ ዝርዝራቸውን በገዙት የጨረታ ሰነድ ላይ ብቻ ሞልተው ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
  6. ተጫራቾች ለሚወዳደሩበት ዕቃ ዋጋው ከቫት ውጭና ከነቫቱ በፊት ተብሎ በጥራት መሞላት ይኖርበታል። እንዲሁም ቫት ከተካተተበት ተካቶበታል ተብሎ እንዲሁም ያልተካተተ ከሆነ አልተካተተም ተብሎ ሊጻፍ ይገባዋል ይህ ሳይሆን ቢቀር ቫት እንደተካተተ አድርጎ /ቤቱ የሚወስድ መሆኑን እናሳውቃለን።
  7. ተጫራቾች የሚጫረቱበትን የጠቅላላ ዋጋ 2% ብር 10,000.00 የጨረታ ማስከበሪያውን በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ ወይም በጥሬ ገንዘብ ከጨረታ ሰነዱ ጋር ማስገባት አለበት ፡፡
  8. ጨረታውን ያሸነፈ ተጫራች ከፖሊ ኮሌጁ ጋር ውል ተዋውሎ የውል ማስከበሪያ የጠቅላላ ዋጋውን 10% ማስያዝ ይኖርበታል፤ በተጨማሪ ያሽነፈበትን ዕቃ 15 ቀናት ውስጥ ለኮሌጁ የማቅረብ ግዴታ አለበት፡፡ ይህ ሳይሆን ቢቀር ለጨረታ ማስከበሪያ ያስያዙት 10% ገንዘብ በቀጥታ ለፖሊ ኮሌጁ ገቢ ሆኖ ከጨረታው የሚሰረዙ ይሆናል፡፡
  9. የጨረታ ሰነዱ ከታህሳስ 03/04/2017 / እስከ ታህሳስ 17/04/2017 ድረስ ባሉት 15 ተከታታይ ቀናት ከኮሌጁ ግዥና ንብረት አስተዳደር ቢሮ ቁጥር 4 በመቅረብ የማይመለስ ብር 100.00 /አንድ መቶ ብር/ በኮሌጁ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በአካውንት ቁጥር GOV 1000019294718 በማስገባትና አድቫይስ በማቅረብ የጨረታ ሰነዱን መግዛት ይጠበቅበታል።፡
  10. ተጫራቾች የሚቀርቡትን የመወዳደርያ ሰነድ ዋናውንና ፎቶ ኮፒውን ለየብቻ ማህተም አሳርፎበት በሰም በታሸገ ኢንቨሎፕ ማቅረብ ይጠበቅበታል፡፡
  11. ጨረታዉ ታህሳስ 18/04/2017 / ከጠዋቱ 330 ታሽጎ ከጠዋቱ 4.00 ሰዓት ላይ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡ በተጫራች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸዉ ባለመገኘታቸዉ የጨረታውን አከፋፈት አያስተጓጉለውም ::
  12. ኮሌጁ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።

ለበለጠ መረጃ በስልከ ቁጥር 0463312719 ወይም 0433613848 ይደውሉ ::

 

የዲላ  ፖሊ  ቴክኒክ  ኮሌጅ

Save Tender