በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የጎንደር መንገድ ጥገና ዲስትሪክት ለአዘዞ-ጎንደር መንገድ ፕሮጀክት አገልግሎት የሚሆን ብዛቱ 9,000 ኩንታል PPC ሲሚንቶ ለሚ ፕላንት ከሚገኘው የናሽናል ሲሚንቶ አ.ማ ፋብሪካ ወደ ጎንደር ከተማ በጨረታ አወዳድሮ ማጓጓዝ ይፈልጋል፡፡
ብሔራዊ ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ
የትራንስፖርት አገልግሎት ግዢ
ጨረታ ቁጥር GN-013/2017
በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የጎንደር መንገድ ጥገና ዲስትሪክት ለአዘዞ-ጎንደር መንገድ ፕሮጀክት አገልግሎት የሚሆን ብዛቱ 9,000 ኩንታል PPC ሲሚንቶ ለሚ ፕላንት ከሚገኘው የናሽናል ሲሚንቶ አ.ማ ፋብሪካ ወደ ጎንደር ከተማ በጨረታ አወዳድሮ ማጓጓዝ ይፈልጋል፡፡
ስለሆነም በጨረታው መሳተፍ የሚፈልጉ በዘርፉ ሕጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸው፣ የዘመኑን ግብር የከፈሉ፣ በጨረታ መሳተፍ የሚያስችል የታክስ ክሊራንስ ማቅረብ የሚችሉ እና የንግድ ምዝገባ ፈቃዳቸው በቂ የጭነት ትራንስፖርት አቅም ያላቸው ስለመሆኑ የሚያረጋግጥ (የመልካም ሥራ አፈፃፀም የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ) ድርጅቶች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 500 በመክፈል በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር እቃ ግዥ ቡድን 1 እና ቡድን 2 ቢሮ ወይንም ጎንደር ከሚገኘው የዲስትሪክቱ ጽ/ቤት መግዛትና መወዳደር የሚችሉ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡
ጨረታው ይህ የጨረታ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 15 ተከታታይ ቀናት ክፍት ሆኖ የሚቆይ ሲሆን ከ15ኛው ቀን ቀጥሎ ባለው የሥራ ቀን ከጠዋቱ 4፡00 ተዘግቶ በዚያው ቀን ከጠዋቱ 4፡30 ተጫራቾች ወይንም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር እቃ ግዥ ዳይሬክቶሬት ቢሮ ይከፈታል፡፡ መ/ቤቱ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር 0911-664 988/0925-356 890 በመደወል ማግኘት ይቻላል፡፡
የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የጎንደር መንገድ ጥገና ዲስትሪክት
