በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 07 አስተዳደር ፋይናንስ ጽ/ቤት የተለያዩ የደንብ ልብሶች፣ የልብስ ስፌት አገልግሎት፣ የፅህፈት መሳሪያዎች፣ የቢሮ ፈርኒቸሮችና ጥገና፣ የአይሲቲ ዕቃዎች ጥገና፣ ቢሮ እና ንብረት ክፍል ፓርቲሽን ጥገና፣ የቢሮ ቀለም ቅብ ስራ፣ ጀነሬተር ጥገና እና መጠነኛ የፋይል መደርደሪያ ስራ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል
የጨረታ ማስታወቂያ
በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 07 አስተዳደር ፋይናንስ ጽ/ቤት
- የተለያዩ የደንብ ልብሶች፣ የልብስ ስፌት አገልግሎት፣
- የፅህፈት መሳሪያዎች፣
- የቢሮ ፈርኒቸሮችና ጥገና፣
- የአይሲቲ ዕቃዎች ጥገና፣
- ቢሮ እና ንብረት ክፍል ፓርቲሽን ጥገና፣
- የቢሮ ቀለም ቅብ ስራ፣
- ጀነሬተር ጥገና እና መጠነኛ የፋይል መደርደሪያ ስራ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል
ስለሆነም
በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልጉ ህጋዊ ተጫራቾች ማሟላት የሚገባቸው መስፈርቶች
1.1.32. ተጫራቾች በመንግስት ግዢ በዕቃ አቅራቢነት ውስጥ የተመዘገቡ እና የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ማቅረብ
ይኖርባቸዋል፡፡
1.1.33. ተጫራቾች እኛ ከሰጠነው የጨረታ ሰነድ የዋጋ ዝርዝር ማቅረቢያ ውጪ ሞልቶ የሚያቀርብ ተጫራች ተቀባይነት
አይኖረውም፡፡
1.1.34. ተጫራቾች ህጋዊ የሆነ የታደሰ የንግድ ስራ ፈቃድ እና የዘመኑን ግብር የከፈሉበትን ሠነድ /ክሊራንስ) ማቅረብ የሚችሉ መሆን አለባቸው፡፡
1.1.35. ተጫራቾች ከስር ከተጠቀሱት ሎቶች ውጪ ለእያንዳንዱ ሎቶች ለጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና አጠቃላይ ያቀረቡትን
ዋጋ 2% በባንክ በተረጋገጠ CPO ብቻ ማስያዝ ይጠበቅባቸዋል፡፡
1.1.36. ለአይሲቲ ጥገና፣ ለፈርኒቸሮች ጥገና አገልግሎት ለጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ብር 5,000.00 (አምስት ሺህ ብር ብቻ) በባንክ በተረጋገጠ CPO ብቻ ማስያዝ ይጠበቅባቸዋል።
1.1.37. ለቢሮ ጥገና፣ ለጀነሬተር ጥገና እና ለፋይል መደርደሪያ ስራ ለእያንዳንዳቸው ብር 20,000.00 (ሃያ ሺህ ብር ብቻ) በባንክ በተረጋገጠ CPO ብቻ ማስያዝ ይጠበቅባቸዋል፡፡
1.1.38 አሸናፊው ተጫራች የውል ማስከበሪያ የውሉን 10%ማስያዝ ይኖርበታል።
1.1.39. ገዢው መስሪያ ቤት በጨረታው ወቅት 25% ሊጨምርም ሊቀንስም ይችላል ፡፡
1.1.40. በተጨማሪም ገዢው ከአሸናፊው ተጫራች ጋር ውል ከተዋዋለበት ቀን ጀምሮ 20% እስከ 6 ወር ባለው ጊዜ ውስጥ ሊጨምር ይችላል፡፡
1.1.41 ተጫራቾች በተሰጣቸው የንግድ ዘርፍ ብቻ መሳተፍ የሚችሉ መሆን አለባቸው ::
1.1.42. ተጫራቾች ናሙናቸውን ከጨረታ መክፈቻው በፊት ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
1.1.43. ተጫራቾች የተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) የተመዘገቡበትን ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ መሆን
አለበት።
1.1.44. ተጫራቾች ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 10 ተከታታይ የስራ ቀናት ውስጥ
ዘወትር በስራ ሰዓት የማይመለስ ብር 400 (አራት መቶ ብር ብቻ ) በመክፈል በቂ/ክ/ከ/የወረዳ 07 ፋይናንስ ጽ/ቤት ውስጥ ሰነዱን መግዛት ይችላሉ።
1.1.45. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዶቻቸውን ዋናውንና ኮፒውን በታሸገ ኤንቨሎፕ በማድረግ ጨረታው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት እለት አንስቶ እስከ 10ኛው ቀን ከቀኑ 11:00 ሰዓት ድረስ ለዚህ ተብሎ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል።
1.1.46. ተጫራቾች ለጨረታው ያቀረቡትን ዋጋ የሚቆይበትን ጊዜ ቢያንስ ለ 60 ቀን መሆኑን መግለጽ ይኖርባቸዋል፡፡
1.1.47. ጨረታው በ11ኛው ቀን ከጠዋቱ በ4፡00 ሰዓት በዓል ከሆነ በቀጣዩ ቀን ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በቂ/ክ/ከ/የወረዳ 07 ፋይናንስ ጽ/ቤት ውስጥ ይከፈታል።
1.1.48. የወረዳው ፋይናንስ ጽ/ቤት የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ማሳሰቢያ፡-
በአ/አ/ከ/አስ/መንግስት ግዢ እና ንብረት አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 17/2002 አንቀፅ 17 ንዑስ 2 እና የግዢ አፈፃፀም መመሪያ ቁጥር 3/2002 አንቀጽ 15 ንዑስ አንቀፅ 20.5 በተደነገገው መሰረት ለጥቃቅን እና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች የጨረታ ሰነድ በነፃ የምንሰጠው በሃገር ውስጥ ምርት ማምረት ዘርፍ ላይ ለተሰማሩ እና በንግድ ዘርፍ ለተሰማሩ ደግሞ በኢንተርፕራይዞቹ ለሚመረቱ ምርቶች ብቻ ልዩ አስተያየት የሚደረግ መሆኑን እንገልፃለን፡፡
ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር፡- 011 515-88-38 አድራሻ፡ ብሄራዊ ከበድሉ ህንጻ
በስተጀርባ ቂርቆስ ክ/ከተማ ወረዳ 7 አስተዳደር ጽ/ቤት 1ኛ ፎቅ
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቂርቆስ ክፍለ
ከተማ ወረዳ 07 አስተዳደር ፋይናንስ ጽ/ቤት
አዲስ አበባ
በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 07 አስተዳደር ፋይናንስ ጽ/ቤት
