Tender Detail

Tender Details

  • Company በወሎ ዩኒቨርሲቲ የላኮመንዛ ንግድና ማማከር ስራዎች ኢንተርፕራይዝ
  • Address ወሎ ዩኒቨርሲቲ ደሴ ካምፓስ ብሎክ 20 ቢሮ ቁጥር 2023 ፡ አማራ ክልል፡ ኢትዯጵያ, Phone: 0914711156
  • Website
  • Deadline28 Jan 2025, 10:00 AM
  • magazine
  • Bid Document Price
  • opening date
  • Categories Accounting & Auditing

በወሎ ዩኒቨርሲቲ የላኮመንዛ ንግድና የማማከር ስራዎች ኢንተርፕራይዝ ከ2008 በጀት ዓመት እስከ 2016 በጀት ዓመት ድረስ ያለውን ሂሳብ መስፈርቱን የሚያሟሉ ኦዲተሮችን በግልጽ ጨረታ‏‏‎‏‏‏‎‏‏‏‏‎‏‎‏ አወዳድሮ ኦዲት ማስደረግ ይፈልጋል።


 

የጨረታ‏‏‎‏‏‏‎‏‏‏‏‎‏‎‏ ማስታወቂያ‏‏‎‏‏‏‎‏‏‏‏‎‏‎‏

የጨረታ‏‏‎‏‏‏‎‏‏‏‏‎‏‎‏ ቁጥር 004/2017

 

በወሎ ዩኒቨርሲቲ የላኮመንዛ ንግድና የማማከር ስራዎች ኢንተርፕራይዝ 2008 በጀት ዓመት እስከ 2016 በጀት ዓመት ድረስ ያለውን ሂሳብ መስፈርቱን የሚያሟሉ ኦዲተሮችን በግልጽ ጨረታ‏‏‎‏‏‏‎‏‏‏‏‎‏‎‏ አወዳድሮ ኦዲት ማስደረግ ይፈልጋል።

ስለሆነም ፣

  1. ተጫራቾች ከሚመለከተው አካል የሙያ ፈቃድ ያላቸው፣ የዘመኑን ግብር የከፈሉ፣ በዘርፉ አግባብ ያለውና የታደሰ ንግድ ፈቃድ፣ የንግድ ምዝገባ የምስክር ወረቀት፣ የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር /ቲን/ የተጨማሪ እሴት ታክስ /ቫት/ ምዝገባ የምስከር ወረቀት፣ የታክስ ክሊራንስ፣ የአቅራቢነት ምዝገባ የምስከር ወረቀት እና ሌሎች አስፈላጊ ተያያዥ ማስረጃዎችን ማቅረብ የሚችሉ መሆን ይኖርባቸዋል።
  2. ተጫራቾች ተቀባይነት ያላቸውን የሂሳብ አያያዝ መርሆዎች መሰረት በማድረግ ኦዲት ማድረግ የሚችሉ መሆን አለባቸው::
  3. ተወዳዳሪዎች የድርጅታቸውን የግል ታሪክ መግለጫ /profile/ ማቅረብ የሚችሉና ቢያንስ አምስት ዓመትና በላይ የስራ ልምድ ያላቸው መሆን አለባቸው።
  4. ተጫራቾች ለጨረታ‏‏‎‏‏‏‎‏‏‏‏‎‏‎‏ ማስከበሪያ የሚሆን በኢትዮጵያ በታወቀ ባንክ የተመሰከረለት የብር 25,000.00 (ሃያ አምስት ሺህ) CPO በድርጅቱ ትክክለኛ ስም ላኮመንዛ ንግድና የማማከር ስራዎች ኢንተርፕራይዝ በማሰራት ወይም በጥሬ ገንዘብ ማስያዝ ይኖርባቸዋል።
  5. ተጫራቾች የጨረታ‏‏‎‏‏‏‎‏‏‏‏‎‏‎‏ ሰነድ መግዣ የማይመለስ ብር 200.00 (ሁለት መቶ) በመክፈል ይህ ማስታወቂያ‏‏‎‏‏‏‎‏‏‏‏‎‏‎‏ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 16ኛው ቀን ከጠዋቱ 400 ድረስ ዘወትር በሥራ ሰዓት‍‍‌‍‍‍‌‍‍‍‍‌‍‌‍ ከኢንተርፕራይዙ አስ/ፋይ/አገ/ዘርፍ ግዥ ቡድን ቢሮ መግዛት ይችላሉ።
  6. ጨረታ‏‏‎‏‏‏‎‏‏‏‏‎‏‎‏ውን የሚያቀርበውና የሚፈርመው ወኪል ከሆነ ከሚመለከተው ውክልና ሰጭ (መዝጋቢ አካል) የተሰጠ ህጋዊ የውክልና ማስረጃ ማቅረብ ይኖርበታል።
  7. ተጫራቾች የድርጅታቸውን የግል ታሪከ መግለጫ /profile/ ለብቻ በማሸግ እና በተጨማሪም የሚሰሩበትን ዋጋ ለብቻ በመሙላት ዋናና አንድ ኮፒ በታሸገ ፖስታ የተጫራቹ ድርጅት ማህተም ተደርጎበትና ተፈርሞ ወሎ ዩኒቨርሲቲ ደሴ ካምፓስ ብሎክ 20 በሚገኘው የኢንተርፕራይዙ አስፋይ አገ ዘርፍ ግዥ ቡድን ቢሮ ለዚሁ በተዘጋጀው የጨረታ‏‏‎‏‏‏‎‏‏‏‏‎‏‎‏ ሳጥን ይህ ማስታወቂያ‏‏‎‏‏‏‎‏‏‏‏‎‏‎‏ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 16ኛው ቀን ከጠዋቱ 400 ሰዓት ድረስ ብቻ ማስገባት አለባቸው።
  8. ጨረታ‏‏‎‏‏‏‎‏‏‏‏‎‏‎‏ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ከላይ በተራ ቁጥር 5 በተጠቀሰው ቀን እና ቢሮ ከረፋዱ 430 በግልፅ ይከፈታል ቀኑ የበዓል ቀን ከሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀን ይከፈታል።
  9. ተጫራቾች ባይገኙም ሰነዳቸው የተሟላ ሆኖ ከተገኘ በሌሉበት የሚከፈት ይሆናል።
  10. ከተጠቀሰው ሰዓት ዘግይቶ የሚመጣ የመወዳደሪያ ሀሳብ ወይም የጨረታ‏‏‎‏‏‏‎‏‏‏‏‎‏‎‏ ሰነድ ተቀባይነት የለውም።
  11. ተጫራቾች አሸናፊ ከሆኑ ምርመራውን ኦዲት ማድረግ የሚችሉት የኢንተርፕራይዙ ዋና /ቤት በሚገኝበት ወሎ ዩኒቨርሲቲ ደሴ ካምፓስ ነው።
  12. አሸናፊ ተጫራች ላሸነፈበት ጠቅላላ ዋጋ 10% በኢትዮጵያ በታወቀ ባንከ የተመሰከረለት CPO ውል ማስከበሪያ በቅድሚያ ማስያዝ ይኖርበታል።
  13. አሸናፊ ተጫራች በውሉ ውስጥ የተካተቱትን ህጐች ማከበር አለበት።
  14. ኢንተርፕራይዙ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታ‏‏‎‏‏‏‎‏‏‏‏‎‏‎‏ውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።

 

ለተጨማሪ ማብራሪያ በስልክ ቁጥር 033 899 8018/15 መጠቀም ይችላል

 

በወሎ  ዩኒቨርሲቲ  የላኮመንዛ  ንግድና  ማማከር  ሥራዎች  ኢንተርፕራይዝ

 

Save Tender