በቦሌ ክ/ከተማ አስተዳደር የማርች 8 የመጀ/ደ/ት/ቤት ሁለተኛ ዙር የግልፅ ጨረታ ማስታወቂያ ቁጥር 002/2017ዓ.ም በጀት ዓመት ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን ዕቃዎች በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
የሁለተኛ ዙር የግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ ቁጥር 002/ 2017 ዓ.ም
በቦሌ ክ/ከተማ አስተዳደር የማርች 8 የመጀ/ደ/ት/ቤት ሁለተኛ ዙር የግልፅ ጨረታ ማስታወቂያ ቁጥር 002/2017ዓ.ም በጀት ዓመት ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን ዕቃዎች በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
በዚህ መሰረት ጨረታውን ለመሳተፍ የሚፈልጉ ህጋዊ ተጫራቾች የሚከተሉትን መስፈርቶች የሚያሟሉ መሆን አለባቸው።
- ተጫራቾች በዘርፉ የተሰማሩበትን ሕጋዊ ፈቃድ ያላቸውንና የዘመኑን ግብር ለመክፈላቸው ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ
- በገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚ/ር በአቅራቢያነት የተመዘገቡና ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ።
- የታደሰ የንግድ ፍቃድ ያላቸው
- ተጨማሪ እሴት ታክስ ምዝገባ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ
- ተጫራቾቾ ከዚህ በታች የተጠቀሰውን የጨረታ ማስከበሪያ በባንክ የተረጋገጠ CPO ማቅረብ አለባቸው።
የተጠየቀው የጨረታ ማስከበርያ በኢትዮጵያ ብር
ሎት 1 ፕላን ማሽነሪ እቃዎች------ብር 9,000
2 ሎት 2 ህንፃ ቁሳቁስና ተገጣጣሚዎች ብር/ 2,000
3 ሎት 2 ህትመት ----ብር/ 3,000
4 ሎት 4 የድንብ ልብስ ስፊት- -ብር/ 2,000
5 ሎት 5 የትምህርት እቃ- -ብር/ 10,000
- የጨረታ ሰነዱን ማስታወቂያው ከወጣበት ቀን ጀምሮ በየሎቱ የማይመለስ 100.00 /አንድ መቶ ብር/በመክፈል የተዘጋጀውን ሰነድ ከተቋሙ ቢሮ ቁጥር 1 እየቀረቡ መግዛት ይቻላል።
- ተጫራቾቾ ጨረታ ከወጣበት ቀን አንስቶ ባሉት 10/አስር/ተከታታይ የስራ ቀናት ቢሮ ቁጥር 3 ድረስ በመምጣት ዋጋው የተሞላበትን የጨረታ ሰነድ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ዋናውንና ፎቶ ኮፒ ለብቻው በማሸግ ለዚሁ ውስጥ ማስገባት አለባቸው፡
- ጨረታው በ10ኛው ቀን 9:00 ታሽጎ በሚቀጥለው ቀን ከቀኑ 4፡00 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል። የጨረታው መዝጊያና መክፈቻ የስራ ቀን ካልሆነ በሚቀጥለው የስራ ቀን በተጠቀሰው ተመሳሳይ ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻችው በተገኙበት ይከፈታል።
- ተጫራቾች ያሸነፉበትን ዋጋ የውል ማስረከቢያ 10% ማስያዝ አለባቸው።
- ተጫራቾች ጨረታው ከመከፈቱ በፊት ለሚወዳደሩበት ናሙና ለሚቀርብባቸው ዕቃዎች ናሙና ማቅረብ አለባቸው። ናሙና የሚደቀርብባቸው ቋሚ ዕቃዎች መስሪያ ቤቱ ባቀረባቸው ስፔስፊኬሽን መሰረት ማቅረብ አለባቸው፡
- የጨረታ አሸናፊ ድርጅት ያሸነፉበትን ዕቃ በራሱ ትራንስፖርት ማርች 8 የመጀ/ደ/ት/ቤት ድረስ ማቅረብ ይኖርበታል።
- መ/ቤቱ ለጨረታ ከቀረበው ዕቃ እስከ 20% የመቀነስም ሆነ የመጨመር መብቱ የተጠበቀ ነው።
- መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው። ተጫራቾች ጨረታውን ስትሞሉ ቫትን ያካተተ መሆን አለበት።
አድራሻ ፡- ጃፓን ኤምባሲ ገባ ብሎ ማርች 8 የመጀ/ደ/ት/ቤት
በቦሌ ክ/ከተማ አስተዳደር የማርች 8 የመጀ/ደ/ት/ቤት
