አዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ በ2017 በጀት ዓመት የእቃ ግዥ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር አ.ማ.ኔ.ብ.ግ.ጨ.008/2017
አዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ በ2017 በጀት ዓመት የእቃ ግዥ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
በዚህም መሠረት ፤
ሎት 1 የሬዲዮ ስቱዲዮ መሳሪያዎች ግዥ በድጋሚ የወጣ
ሎት 2 55 inch television ግዥ በድጋሚ የወጣ
በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት የሚፈልግ በመሆኑ በጨረታው ለመሳተፍ የምትፈልጉ ተጫራቾች፡-
- በዘርፉ የታደሰ ንግድ ያላቸው፤ የዘመኑን የዘመኑን ግብር የከፈሉና የነቢዎች ክሊራንስ ያላቸው።
- የተጨማሪ እሴት ታክስ፣ የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር፣ የምዝገባ ሰርተፍኬት ማቅረብ የሚችሉና በግዥ አቅራቢነት የተመዘገቡ፡፡
- ተጫራቶች በሚያቀርቡት እያንዳንዱ ሰነድ እና ፖስታ ላይ የድርጅቱን ማህተምና ፈርማቸውን ማኖር ይጠበቅባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች ለሚያቀርቡት አጠቃላይ ዋጋ ለእያንዳንዱ ሎት ማለትም ለሎት 1 የጨረታ ማስከበሪያ ብር 100,000.00፤ ለሎት 2 የጨረታ ማስከበሪያ ብር 150,000.00 በባንክ በተረጋገጠ ሲፒአ ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች የጨረታውን ዝርዝር የሚያሳይ የጨረታ ሰነድ ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለሎት 1 ጨረታ 20 የስራ ቀናት ለሎት 2 ጨረታ 10 የስራ ቀናት ውስጥ አዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ ቢሮ ቁጥር 28 በመገኘት የማይመለስ ብር ለእያንዳንዱ ለሎት 1 እና ለሎት 2 ብር 300.00 /ሦስት መቶ ብር/ በመክፈል ዘወትር በሥራ ሰዓት መግዛት ይችላሉ
- የሎት 1 ጨረታ የሚከፈተው በ21ኛው ቀን ሲሆን የሎት 2 ጨረታው የሚከፈተው በ11ኛው ቀን ከጠዋቱ 4፡00 ተዘግቶ በዚሁ ቀን ከጠዋቱ 4፡30 ተጫራቾች ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በአዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ ቢሮ ቁጥር 06 ይከፈታል፡፡ ሆኖም ግን የተጫራቾች አለመገኘት ጨረታውን ከመከፈት አያግደውም፡፡ የመክፈቻው ዕለት በዓል/ዕረፍት ቀን ከሆነ በቀጣዩ የስራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ተዘግቶ ይከፈታል፡፡
- ተጫራቾች የመወዳደሪያ ሃሳባቸውን ዋናውንና ኮፒውን / ቴክኒካል ኦሪጅናልና ኮፒ፣ ፋይናንሻል ኦሪጅናልና ኮፒ በተለያየ ፖስታ በማሸግ ለዚሁ ተብሎ በተዘጋጀ የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይጠበቅባቸዋል፡፡
- በአንዱ ተጫራች ዋጋ ላይ ተንተርሶ ዋጋ ማቅረብ የተከለከለ ነው፡፡
- በጨረታ ያሸነፈ ተጫራች ከመ/ቤታችን ጋር ጨረታውን እንዳሸነፈ ካወቀበት ጊዜ አንስቶ በ15 ቀናት ውስጥ በሲፒኦ የጠቅላላ ዋጋውን 10% በማስያዝ ውል መዋዋል ይኖርበታል፡፡
- ተቋሙ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
አድራሻ ፡-
የአዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ 5 ኪሎ ቅድስት ማሪያም ቤ/ክርስቲያን ከማህበረ ቅዱሳን ጀርባ ያለው ህንፃ።
ለበለጠ መረጃ ስልክ ቁጥር ፡- 011 1 11 63 82 መደወል ይችላሉ፡፡
የአዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ
