በዲላ ከተማ አስተዳደር በማዘጋጃ ቤት በUllDP ፕሮግራም በ2017 በጀት ዓመት የኤሌክትሮኒክስ ቋሚ ዕቃዎች ግዥ በቀረበው ዝርዝር መሠረት አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
በግልጽ የጨረታ ማስታወቅያ
በዲጋሚ የወጣ የቋሚ ዕቃዎች ገዥ ጨረታ ማስታወቅያ
በዲላ ከተማ አስተዳደር በማዘጋጃ ቤት በUllDP ፕሮግራም በ2017 በጀት ዓመት የኤሌክትሮኒክስ ቋሚ ዕቃዎች ግዥ በቀረበው ዝርዝር መሠረት አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል። ስለዚህ በንግዱ ሥራ ዘርፍ ህጋዊ ፍቃድ ያላቸው ድርጅቶች መወዳደር ይችላሉ፡፡
የጨረታ ቁጥር DILLA UIIDP-Goods/001/2024/25 ኤሌክትሮኒክስ
- የታደሰ ንግድ ፍቃድ ያላቸው
- የንግድ ምዝገባ ም/ወረቀት ያላቸው
- የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋብ የሆኑ
- የአቅራቢነት ምዝገባ ም/ወረቀት ያለው
- የግብር ከፋይ ምዝ/ምስክር ወረቀት
- ግብር ስለመክፈላቸው ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ
- ተጫራቾች ለጨረታ ዋስትና በባንክ የተረጋገጠ ለእያንዳንዱ የ50,000 /ሃምሳ ሽህ ብር/ CPO ማቅረብ ይኖርባቸዋል
- ተጫራቾች ይህ ማስታወቅያ ከወጣበት ዕለት ጀምሮ ዘወትር በሥራ ቀናት የማይመለስ ብር 200 /ሁለት መቶ ብር/ መክፈል በጽ/ቤታችን ቢሮ ቁጥር 6 ቀርበው ሰነዱን መውሰድ ይችላሉ።
- ዘግይቶ የመጣ ፖሰታ ተቀባይነት የለዉም
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ቴክኒክል 1 ኦርጅናል 2 ቴክኒካል ኮፒ ለየብቻ በማሸግ ፋይናንሻል 1 ኦርጅናል እና 2 ፋይናንሻል ኮፒ እያንዳንዱን ለየብቻ በማሸግ በመጨረሻ ሁሉንም በአንድ እናት በኤንቨሎፕ በታሸገ ፖስታ የድርጅቱን ህጋዊ ማህተም በማድረግ አድራሻችዉን በመሙላት በጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል።
- ተጫራቾች ይህ ማስታወቅያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን አንስቶ ለ15 ተከታታይ ቀናት ቆይቶ በ16ኛው ቀን የሚከፈት ሲሆን 16ኛው ቀን የሥራ ቀን ካልሆነ በቀጣይ የሥራ ቀን ከጠዋቱ 3፡00 ታሽጎ ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ወኪሎቻቸው በተገኙበት የሚከፈት መሆኑን እንገልጻለን።
መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ በህግ የተጠበቀ ነው፡፡
በጌዴኦ ዞን የዲላ ከተማ ፋይ/ጽ/ቤት
