በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የጅማ መንገድ ጥገና ዲስትሪክት ለሠራተኞች አገልግሎት የሚውል የሥራ ጫማዎችና የደንብ ልብሶች በጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡
የሠራተኞች ጫማና የደንብ ልብስ
የጨረታ ማስታወቂያ
ማስታወቂያ ቁጥር ፡- T- 05/2017
በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የጅማ መንገድ ጥገና ዲስትሪክት ለሠራተኞች አገልግሎት የሚውል የሥራ ጫማዎችና የደንብ ልብሶች በጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡
በዚሁ መሠረት ተጫራቾች ፡-
- በዘርፉ የታደሰ ሕጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸው ፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ የሆኑ፡፡
- ተጫራቾች የጨረታውን ዝርዝር መግለጫ ሠነድ ጨረታው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ጅማ ዋናው ዩኒቨርሲቲ በስተግራ በሚገኘው በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ጅማ መንገድ ጥገና ዲስትሪክት ግዥ አቅርቦትና ንብረት አስተዳደር ቢሮ ቁጥር 04 የማይመለስ አራት መቶ ብር (400.00) ብቻ በመክፈል ሠነዱን መውሰድ ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የሚያቀርቡት ዕቃ ጥራቱን የጠበቀ ስለመሆኑ ናሙና ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች የዕቃዎችን ዝርዝር እና የጨረታ ማወዳደሪያ ሠነዳቸው ላይ ስማቸውን በትክክል ለይቶ በመፃፍ ፊርማቸውን እና አድራሻቸውን በማስፈር እና ማህተም በማድረግ ማስታወቂያው ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት ተከታታይ የሥራ ቀናት ቅዳሜን ጨምሮ ማስገባት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የሚጫረቱበትን ዋጋ በጨረታ ሠነድ ውስጥ በተያያዘው የዋጋ መሙያ ቅፅ ለይቶ በመሙላት የድርጅታቸውን ማህተምና የተወካይ ፊርማ በማድረግ በታሸገ ኤንቨሎፕ ቴክኒካልና ፋይናንሽያል በኮፒ እና በኦርጂናል በተለያየ ኤንቨሎፕ ዶክመንቱን በማቅረብ ይህ ጨረታ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በተጠቀሰው አድራሻ እና ለዚሁ ጉዳይ በተዘጋጀ ሣጥን ማስገባት ይችላሉ።
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ 60,000.00 (ስልሳ ሺህ) ብር ብቻ በባንክ በተመሰከረ ሲፒኦ (CPO) ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
- ጨረታው ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት የካቲት 29 ቀን 2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ታሽጎ በዕለቱ 4፡30 ሰዓት ጅማ ዲስትሪክት ቅጥር ግቢ በሚገኘው የሠራተኞች መሰብሰቢያ አዳራሽ ይከፈታል፡፡
- ዲስትሪክቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
- ለበለጠ መረጃ፡- ተጫራቾች የሚከተለውን አድራሻ መጠቀም ይችላሉ፡፡
የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ጅማ መንገድ ጥገና ዲስትሪክት
ግዥ አቅርቦትና ንብረት አስተዳደር
ስልክ ቁጥር 047-211-34-83 ጅማ
የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር
