የአፋር ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ አገልግሎት ለምዝገባ ስራ የሚውል ህትመት በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ማሳተም ይፈልጋል፡፡
ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ሰነድ ቁጥር 001/2017
የአፋር ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ አገልግሎት ለምዝገባ ስራ የሚውል ህትመት በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ማሳተም ይፈልጋል፡፡
ስለዚህ በጨረታው ለመካፈል የሚፈልጉ እና ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች ማሟላት የሚችሉ ተጫራቾች ቀርበው እንዲወዳደሩ ይጋብዛሉ፡፡
- ተጫራቾች የዘመኑን የመንግስት ግብር የከፈሉና የንግድ ፈቃዳቸውን ያሳደሱ።
- በዘርፉ ለተሰማሩበት ስራ አግባብነት ያለው የብቃት ማረጋገጫ ሰርተፍኬት ማቅረብ የሚችሉ።
- የግብር ከፋይ ቲን ነምበር ያላቸው መሆን አለበት።
- ተወዳዳሪዎች ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ5 ተከታታይ ቀናት የማይመለስ 200 (ሁለት መቶ ብር) ወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ አገልግሎት ግ/ፋ/ን/ አስ የጨረታ ሰነዱን ግዥ መፈጸም ይችላሉ።
- ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት 6ተኛው ቀን ማለትም ከጠዋቱ 2፡00 ፖስታው በሰም ታሽጎ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ገቢ ከሆነ በኋላ ተዘግቶ ልክ በዚያው ቀን 2፡30 ሰዓት ላይ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል። ተዘግቶ የሚከፈትበት ቀን የስራ ቀን ካልሆነ በቀጣይ ቀን የሚከፈት ይሆናል።
አገልግሎቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ሙሉ በሙሉ ሆነ በከፊል ጨረታውን የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር:- 0336660883 ደውለው ይጠይቁ
የአፋር ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ አገልግሎት
