መ/ቤታችን የሂሳብ ምርመራ አገልግሎት ኮርፖሬሽን ካዛንችስ ከሲንቄ ባንክ ፊት ለፊት የሚገኘውን የህንፃውን ምድር ወለል 173 ሜትር ካሬ ለተለያዩ አገልግሎቶች የሚውል ክፍል ማከራየት ይፈልጋል።
የጨረታ ማስታወቂያ
መ/ቤታችን የሂሳብ ምርመራ አገልግሎት ኮርፖሬሽን ካዛንችስ ከሲንቄ ባንክ ፊት ለፊት የሚገኘውን የህንፃውን ምድር ወለል 173 ሜትር ካሬ ለተለያዩ አገልግሎቶች የሚውል ክፍል ማከራየት የሚፈልግ በመሆኑ ተጫራቾች ከዚህ በታች የተገለፁትን መስፈርቶች የሚያሟሉ መወዳደር የሚችሉ መሆኑን ይገልፃል፡፡
- የዘመኑን ግብር የከፈለ እና የታደሰ ንግድ ፈቃድ ያለው፤
- ተጨማሪ እሴት ታክስ ከፋይ ለመሆናቸው የሚያረጋግጥ የምዝገባ የምስክር ወረቀት አግባብ ካለው ሕጋዊ አካል ማቅረብ የሚችል፤
- የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችል፤
- በመንግስት ጨረታዎች መሳተፍ የሚያስችል ማረጋገጫ የምዝገባ ምስክር ወረቀት አግባብ ካለው ሕጋዊ አካል ማቅረብ የሚችሉ፤ (Tax Clearance)
- የጨረታ ማስከበሪያ ብር 50,000 /ሃምሳ ሺህ ብር/ በሲፒኦ ማስያዝ ይኖርባቸዋል፤
- ተጫራቾች አንዱን ሜትር ካሬ ከተጨማሪ እሴት ታክስ በፊት ወይም የተጨማሪ እሴት ታክስን ጨምሮ በታሸገ ኢንቨሎፕ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፤
- ተጫራቾች ጨረታውን ቢያሸንፉ የሚከራዩትን ክፍሎች ለምን አገልግሎት እንደሚያውሉት በግልጽ የሚያሳይ እቅድ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፤
- ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ቅዳሜና እሁድን ሳይጨምር በኮርፖሬሽኑ የሥራ ሰዓት ለአስር ተከታታይ የሥራ ቀናት ክፍት ሆኖ ይቆያል፤
- ጨረታው በ11ኛው የሥራ ቀን ላይ ከጠዋቱ በ4፡00 ሰዓት ላይ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይታሸጋል፡፡ በዕለቱ በ4፡30 ሰዓት ላይ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት የጨረታው ሰነድ ይከፈታል፡፡
- ኮርፖሬሽኑ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ይሁን ሙሉ በሙሉ የመቀበልም ሆነ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ለበለጠ መረጃ-በስልክ ቁጥር 011 553 79 27/ 011 553 50 15
የሂሣብ ምርመራ አገልግሎት ኮርፖሬሽን
