በሰሜን ሸዋ ዞን የዘመሮ ከተማ መሪ ማዘጋጃ ቤት በ2017 ዓ.ም በጀት አመት በከተማው የውስጥ ለውስጥ መንገድ በጨረታ አወዳድሮ ለማሰራት ግሬደር፣ እስካቫተር፣ ሮሎ እና ገልባጭ መከራየት ይፈልጋል፡፡
የጨረታ ማስታወቂያ
ቁጥር ማዘግ/ፋ/142/2017
በሰሜን ሸዋ ዞን የዘመሮ ከተማ መሪ ማዘጋጃ ቤት በ2017 ዓ.ም በጀት አመት በከተማው የውስጥ ለውስጥ መንገድ በጨረታ አወዳድሮ ለማሰራት ግሬደር፣ እስካቫተር፣ ሮሎ እና ገልባጭ መከራየት ይፈልጋል፡፡ በመሆኑም ህጋዊ ፈቃድ ያላቸውና ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾች መወዳደር የሚችሉ መሆኑን እንገልጻለን፡፡
- በዘርፉ በዘመኑ የታደሰ ህጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸው፤
- የዘመኑን ግብር የከፈሉ ለመሆናቸው ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፤
- የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር /ቲን/ ያላቸው፤ የሚጫረቱት ጨረታ ከ200,000 ብር በላይ ከሆነ የቫት ተመዝጋቢ መሆን አለባቸው::
- ተጫራቾች በጨረታ ለመሳተፍ ከላይ በተ.ቁ 1-3 የተጠቀሱትንና የሚመለከታቸውን ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከመጫረቻ ሰነዶቻቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው::
- የሚያቀርቡትን አይነትና ዝርዝር መግለጫ /ስፔስፊኬሽን/ ከጨረታ ሰነዱ ማግኘት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 200 /ሁለት መቶ ብር/ በመክፈል ከግ/ፋ/ን/አስ/ቡድን ቢሮ ቁጥር 4 ማግኘት ይችላሉ፡፡
- የጨረታ ሰነድ የሚሸጥበት ጊዜ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ 15 ቀን ሆኖ በ15ኛው ቀን እስከ ቀኑ 11፡00 ሰአት ድረስ ነው::
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና /ቢድ ቦንድ/ ለሚወዳደሩበት ጠቅላላ ዋጋ 2 ፐርሰንት በጥሬ ገንዘብ፣ በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትእዛዝ /ሰ.ፒ.ኦ/ ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ወይም በጥሬ ገንዘብ ማስያዝ አለባቸው::
- አሸናፊ የሆነው ድርጅት አሸናፊነቱ እንደተገለጸ በ5 ተከታታይ የስራ ቀናት የውል ማስከበሪያ የውሉን ዋጋ 10 በመቶ በማስያዝ ውል መፈጸም አለበት፡፡
- አሸናፊው የሚለየው በጥቅል ዋጋ ስለሆነ ሁሉንም መሙላት አለባቸው::
- ማንኛውንም ወጭ ፣ ብልሽት ፣ በራሱ ወጪ ሸፍኖ መስራት የሚችል፡፡
- የሚያቀርቡት እቃ /ማሽን/ ጥራትና ብቃት ያለው መሆን አለበት፡፡
- ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ሃሳቡን በአንድ ወይም አንድ ወጥ በሆነ ሁለት ቅጂዎች ማለትም ዋናና ቅጂ በማለት በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ በግ/ፋ/ን/አስ/ቡድን ወይም ቢሮ ቁጥር 4 በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ዘወትር በስራ ሰዓት ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ 15 ቀን ሆኖ በ15ኛው ቀን እስከ ቀኑ 11፡00 ድረስ ማስገባት ይኖርበታል፡፡
- ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በግ/ፋ/ን/አስ/ቡድን ክፍል በ16ኛው ቀን ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ይከፈታል፤ ሆኖም ግን 16ኛው ቀን በዓል ከሆነ በሚቀጥለው ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ይከፈታል፡፡
- መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው::
- በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልጉ ስለጨረታው ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ ቢሮ ቁጥር 4 ድረስ በአካል በመገኘት ማግኘት ይችላሉ፡፡
በአብክመ በሰሜን ሸዋ ዞን የዘመሮ ከተማ መሪ ማዘጋጃ ቤት
