የደ/ም/ኢ/ህ/ክ/ መንግስት ካፋ ዞን ቦንጋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በ2017 ዓ/ም በጀት ዘመን ለተሽከርካሪዎች ስልጠና አገልግሎት የሚውሉ ዕቃዎችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
የግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ
የደ/ም/ኢ/ህ/ክ/ መንግስት ካፋ ዞን ቦንጋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በ2017 ዓ/ም በጀት ዘመን ለተሽከርካሪዎች ስልጠና አገልግሎት የሚውሉ ዕቃዎችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
ስለሆነም፡ ተወዳዳሪዎች
1ኛ በሙያ መስክ ወይም በዘርፉ የተመዘገቡና ለዘመኑ የታደሰ ንግድ ፍቃድ ያላቸው ፣ የዘመኑን ግብር የከፈሉ ስለመሆናቸው ህጋዊ ዕቃ አቅራቢ ዝርዝር ውስጥ ስለመመዝገባቸው የተጨማሪ እሴት ታክስ /VAT/ ከፋይ ስለመሆናቸው እና የምዝገባ ምስክር ወረቀት ማስረጃ ፎቶ ኮፒ ከጨረታ ሰነድ ጋር በማያያዝ ማቅረብ አለባችው::
25 የዕቃው ዝርዝር መግለጫ /specification/ የያዘውን የጨረታ ሰነድ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ከ1ኛ ቀን ጀምሮ ለ14 ተከታታይ ቀናት ቅዳሜና እሁድን ጨምሮ አዲስ አበባ ሜክሲኮ አካባቢ ባለው ፖሊ ቴክኒክ ት/ቤት አካባቢ እና ቦንጋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ግዥግብ/ አስተዳደር ቢሮ ቁጥር 01 በአካል በመቅረብ በኮሌጁ የሂሳብ ቁጥር 1000029122877 ላይ የማይመለስ 200 ብር በማስገባት የመጫረቻ ሰነዱን መውሰድ ትላላችሁ ፡፡
3ኛ የምጫረቱባቸውን እቃዎች በመለየት በአይነታቸው እያንዳንዱን የሚሸጡበትን ዋጋ በሰም በታሸገ ኤምቨሎፕ ለየብቻ ዋናና ኮፒውን በፖስታ በማሸግ የሚጫረቱበትን ዘርፍ የተጫራቶችን ስም ወይም ድርጅት በመፃፍና ማህተም በመምታት የጨረታ ማስታውቂያ በጋዜጣ ከወጣበት 1ኛ ቀን ጀምሮ ለ14 /አስራ አራት/ ተከታታይ ቀናት ወይም ጨረታ የሚታሸግበት ቀንና ሰዓት ድረስ የጨረታ ሰነዱን በገዙበት ቢሮ ለዚሁ ተግባር በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
4ኛ ለጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ብር 10,000 (አስር ሺህ ብር ) በባንክ የተረጋገጠ ሲፒኦ ብቻ የጨረታ ማወዳደርያ ሰነድ ማስያዝ የሚጠበቅባቸው ሲሆን ቢድ ቦንድ እና ቼክ የማንቀበል መሆኑን እናሳስባለን፡፡
5ኛ አሸናፊዎች ባሸነፉበት የዕቃ ዋጋ መጠን የውል ማስከበሪያ 10% በባንክ የተረጋገጠ CPO ብቻ ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡ በጨረታ የተሸነፉ ተወዳዳሪዎች ለጨረታ ማስከበሪያ ያስያዙት ሲፒኦ ወዲያውኑ ይመለስላቸዋል፡፡
6ኛ አሸናፊ ተጫራቾች ዕቃውን እስከ ቦንጋ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ድረስ የትራንስፖርትና ማንኛውን ወጪ በመቻል በውሉ ላይ በሚጠቀሰው ቀን ማቅረብና ማስረከብ አለባችው፡፡ ለማያቀርቡ ለውል ማስከበርያ ያስያዙት CPO አይመለስም፡፡
7ኛ የጨረታ ሳጥን የሚታሸገው የጨረታ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት 15ኛው ቀን ከቀኑ 9:30 እስከ 10:00 ሰዓት ላይ ይሆናል፡፡ 8ኛ ጨረታው ፀንቶ የሚቆይበት ጊዜ ከተከፈተበት እለት ጀምሮ ለ30 ቀናት ይሆናል፡፡
9ኛ የጨረታ ሳጥን የሚከፈተው ቦንጋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ግቢ ውስጥ ግዥ ንብ /አስ/ር ቢሮ ቁጥር 01 ጋዜጣ ከወጣበት ልክ በ17ኛው ቀን ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ላይ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት የሚከፈት ይሆናል፡፡ ሆኖም በጨረታ መክፈቻ ወቅት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪል ያለመገኘት ጨረታውን ከመከፈት አይከለክልም፡፡ እለቱ የእረፍት ወይም በዓል ቀን ከሆነ ወደ የሚቀጥለው ስራ ቀን ይተላለፋል፡፡
10ኛ በጨረታ ሰነዱ ላይ ማንኛውንም ማስተካከያ ማድረግም ሆነ ከቀረበው ሰነድ ውጭ መፃፍ አይፈቀድም።
11ኛ ተጫራቾች ባሸነፉበት እቃ የካሽ ሪጅስቴር ደረሰኝ ከአታችሜንት ጋር አያይዞ ማቅረብ ወይም የካሽ ሪጅስቴር ደረሰኝ የማይጠቀሙ ከሆነ የማይጠቀሙበት ምክኒያት ከገቢዎች መ/ቤት ደብዳቤ በማስደገፍ የእጅ በእጅ ደረሰኝ ጋር ማቅረብ አለባችሁ፡፡
12ኛ ኮሌጁ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው::
ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር 0917916439/091346623/ ደውለው መጠየቅ ይቻላል፡፡
የደ/ም/ኢ/ህ/ክ/ መንግስት ካፋ ዞን ቦንጋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ
