የሀላባ ዞን ፋይናንስ መምሪያ በዞን አስተዳደር ቅጥር ግቢ ውስጥ የሚገኙ ያገለገሉ መኪና ፣ ሞተር ሳይክሎች እና የኤሌክትሮኒክስ እቃዎችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል፡፡
ያገለገሉ ተሽከርካሪዎች እና ኤሌክትሮኒክስ ሽያጭ ማስታወቂያ
የሀላባ ዞን ፋይናንስ መምሪያ በዞን አስተዳደር ቅጥር ግቢ ውስጥ የሚገኙ ያገለገሉ መኪና፣ ሞተር ሳይክሎች እና የኤሌክትሮኒክስ እቃዎችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል፡፡
ስለሆነም በጨረታው መሳተፍ የሚፈልጉ ተጫራቾች፡-
- መኪኖች፤ ሞተር ሳይክሎች እና የኤሌክትሮኒክስ እቃዎች የሚገኙበት አድራሻ ዞን አስተዳደር ቅጥር ግቢ ውስጥ ይገኛል።
- ተጫራቾች የጨረታ ዋጋቸውን ከማቅረባቸው በፊት መኪኖች፣ ሞተርሳይክሎች እና የኤሌክትሮኒክስ እቃዎች ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት የስራ ቀናት በአካል በመገኘት ከላይ በተገለፀው አድራሻ አስቀድመው ማየት የሚችሉ ሲሆን በጨረታው ሰነድ ላይ ካለው መረጃ በአካል ቀርበው ሲመለከቱ ልዩነት ካለ እና ይህንኑ ሲያረጋግጡ ጨረታው ከመዘጋቱ ከ5 የስራ ቀናት በፊት ለመምሪያው ማሳወቅ አለባቸው።
- በጨረታው ማንኛውም ኢትዮጵያዊ የሆነ ግለሰብ ወይም ድርጅት መሳተፍ ይችላል፡፡
- ተጫራቾች የሚዝዙበትን የተሽከርካሪ ኤሌክትሮኒክስ በጨረታ መነሻ ዋጋ ሳይሆን በሚገዙበት መግዣ ዋጋ 10% የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና በባንክ የተረጋገጠ CPO በማቅረብ በጨረታው መሳተፍ ይችላሉ። ተጫራቾች ጨረታው ከተከፈተ በኋላ ከውድድሩ ቢወጡ ለጨረታ ማስከበሪያ ያስያዙት ገንዘብ ለመንግስት ገቢ ይሆናል፡፡ የጨረታ ማስከበሪያ በጨረታው ያሸነፈ ተጫራች እንደተመረጠ ወዲያውኑ ጨረታውን ላላሸነፉ ተጫራቾች በቀጣይ 5 የስራ ቀናት ተመላሽ ይደረጋል፡፡
- ስለአሻሻጡ የተዘጋጀውን የመኪና፣ የሞተርሳይክሎች እና የኤሌክትሮኒክስ እቃዎች ዝርዝር መረጃ የያዘ ሰነድ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በተከታታይ 15 የስራ ቀናት ውስጥ በመምሪያው ግዥና ፋይናንስ ንብረት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ቢሮ ቁጥር 2 ለእያንዳንዱ የማይመለስ 200 /ሁለት መቶ ብር/ በመክፈል ሰነዱን መግዛት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች መግዛት የሚፈልጉትን ተሽከርካሪ እና ኤሌክትሮኒክስ ዋጋ በታሸገ ኤንቨሎፕ 1 ኦርጅናል እና ኮፒ በማዘጋጀት ከላይ ሙሉ አድራሻውን በመፃፍ ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን እስከ 15ኛው የስራ ቀን ውስጥ ከቀኑ 11፡30 በመምሪያው በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ማስገባት ይችላሉ።
- ጨረታው በጋዜጣ በወጣ በ16ኛው የስራ ቀን ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት ታሽጎ 4፡30 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በግልጽ የሚከፈት ይሆናል፡፡
- ተጫራቾች በጨረታው ያሸነፉበትን ያገለገሉ ተሽከርካሪዎች እና የኤሌክትሮኒክስ ሙሉ ክፍያውን በ15 የስራ ቀናት ውስጥ በመክፈል ማንሳት አለባቸው በተጠቀሰው ጊዜ ገደብ ውስጥ ካላነሱ ያስያዙት ገንዘብ ለመንግስት ገቢ ይሆናል፡፡
- መምሪያው የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይንም በከፊል የመሰረዝ ሙበቱ የተጠበቀ ነው።
ለበለጠ መረጃ ስልክ 0912122421
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሀላባ ዞን ፋይናንስ መምሪያ
