በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ስር የሚገኘው የራስ ኃይሉ ስፖርት ትምህርትና ስልጠና ማዕከል ለስፖርት ባርና ሬስቶራንት አገልግሎት ላይ የሚውል 164.3 ካሬ ሜትር ስፋት ያለውን ንግድ ቤት ለሚፈልጉ ተጫራቾች በጨረታ አወዳድሮ ለ3 አመት ማከራየት ይፈልጋል።
በድጋሚ የወጣ የስፖርት ባርና ሬስቶራንት ግልፅ
የጨረታ ማስታወቂያ ጨረታ ቁጥር 02/2017 ዓ.ም
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ስር የሚገኘው የራስ ኃይሉ ስፖርት ትምህርትና ስልጠና ማዕከል ለስፖርት ባርና ሬስቶራንት አገልግሎት ላይ የሚውል 164.3 ካሬ ሜትር ስፋት ያለውን ንግድ ቤት ለሚፈልጉ ተጫራቾች በጨረታ አወዳድሮ ለ3 አመት ማከራየት ይፈልጋል። በመሆኑም ከታች የተገለጸውን መስፈርት የሚያሟሉ ተጫራቾችን በማወዳደር ወደ ስራ ማስገባት ይፈልጋል።
በዚሁ መሰረት በጨረታው መሳተፍ የሚፈልጉ ተጫራቾች ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች ማሟላት ይኖርባቸዋል።
- ተጫራቾች ከጨረታ ሰነድ ጋር ማንነታቸውን የሚገልፅ ትክክለኛነቱ የተረጋገጠ መታወቂያ ፎቶ ኮፒ ማያያዝ ይኖርባቸዋል።
- በዋጋ ማቅረቢያ ሰነድ ላይ የተጫራቹ ወይም የህጋዊ ወኪሉ ስም እና ፊርማ ማህተም ያረፈበት መሆን አለበት።
- ተጫራቾች የሚያቀርባቸው የጨረታ ሰነድ በራስ ኃይሉ የስፖርት ትምህርትና ስልጠና ማዕከል 1ኛ ፎቅ ላይ ከአስ/ፋይናንስ ቢሮ ቁጥር 2 ቀርበው የማይመለስ ብር 300.00 /ሶስት መቶ/ ብር ከፍለው መግዛት ይጠበቅባቸዋል።
- ተጫራቾች የገዙትን የጨረታ ሰነድ በመሙላት ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 10 ተከታታይ የስራ ቀናት ውስጥ ሰነዱን በታሸገ ኤንቨሎፕ ኦርጅናል ፎቶ ኮፒ አድርጎ በተዘጋጀው የጨረታ ሰነድ ሳጥን ውስጥ መጨመር ይኖርባቸዋል።
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በወጣቶችና ስፖርት ቢሮ የራስ ኃይሉ የስፖርት ትምህርትና ስልጠና ማዕከል ስም የተሰራ ሲፒኦ 50,000 /ሃምሳ ሺህ ብር/ ከጨረታ ፖስታ ጋር ማስገባት ይኖርባቸዋል።
- ተጫራቾች ከገዙት ጨረታ ሰነድ ውጭ ተሞልተው ለሚመጡ ሰነድ ተቀባይነት የለውም።
- ጨረታው ማስታወቂያው ከወጣበት በአስረኛው የስራ ቀን 8:00 ላይ ታሽጎ 8፡30 ላይ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በራስ ኃይሉ የስፖርት ትምህርትና ስልጠና ማዕከል 1ኛ ፎቅ ላይ በግልፅ ይከፈታል።
- ከተባለው ቀንና ሰአት በኋላ የሚመጣ የጨረታ ሰነድ ውድቅ ይሆናል።
- መስሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
አድራሻ፡- አዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ህንፃ አጠገብ ወይንም ከመድኃኔዓለም አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ከሚገኘው አደባባይ ወደ ግሩም ሆስፒታል በሚወስደው አስፋልት መንገድ በስተግራ 100 ሜትር ገባ ብሎ።
የአ/አ ከተማ አስተዳደር ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ የራስ ኃይሉ ስፖርት ትምህርትና ስልጠና ማእከል
