Tender Detail

Tender Details

  • Company Addis Ababa City Administration Public Recreational Areas Corporation (የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የህዝብ መዝናኛ ቦታዎች አስተዳደር ኮርፖሬሽን)
  • Address ቦሌ ፡ አዲስ አበባ ፡ ኢትዮጵያ, Phone: 0115572949
  • Websitehttps://aacaprac.gov.et/?lang=ahm
  • Deadline12 Jun 2025, 12:00 AM
  • magazine
  • Bid Document Price
  • opening date2025-06-12 00:00:00
  • Categories Land, House, Building And Warehouse Rent

የህዝብ መዝናኛ ቦታዎች አስተዳደር ኮርፖሬሽን በስሩ ያሉትን ለተለያዩ ፓርኮች ሙሉ ለሙሉ ለሶስተኛ ወገን በማስተላለፍ እንዲተዳደር ለማከራየት በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ በኪራይ ማስተላለፍ ይፈልጋል፡፡


 

ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ የጨረታ ቁጥር 73/2017

 

የህዝብ መዝናኛ ቦታዎች አስተዳደር ኮርፖሬሽን በስሩ ያሉትን ለተለያዩ ፓርኮች ማለትም

  • ሎት 1:- የህዝብ መዝናኛ ቦታዎች አስተዳዳር ኮርፖሬሽ በውስጡ የሚያስተዳድራቸው በኮሪደር ልማት የለሙ በካሳንችስ ሳር ቤት ለቡ ጀሞ መካኒሳ ጀርመን አደባባይ 4 ኪሎ 5 ኪሎ፣ ስድስት ኪሎ 24 ቀበሌ አካባቢ 22 አካባቢ መገናኛ ለም ሆቴል አካባቢ ለሚኩራ ሰሚት አቦ ማዞሪያ ቄራ ጎሮ ሂልተን አካባቢ፣ ብስራተ ገብኤል አንበሳ ጋራጅ ገርጂ መብራት ሀይል፣ ሽሮ ሜዳ አካባቢ የሚገኙ የተለያዩ ፓርኮችን ለማከራየት
  • ሎት 2:- ኮልፌ ፓርክ ውስጥ የሚገኙ ሱቅና አዳራሽ፣ አቃቂ ፓርክ ውስጥ የሚገኙ ካፌና አዳራሽ፣በከንቲባ ቢትወደድ ፓር ውስጥ የሚገኙ ካፌና ሱቆችን አምባሳደር ፓር ውስጥ የሚገኙ ካፌዎችን እንዲሁም ሸገር ፓርክ ውስጥ የሚገኙ ሱቆችን ለማከራየት
  • ሎት 3:- በፈረንሳይ ፓር የችግኝ ጣቢያውን ሳይጨምር ሙሉ ለሙሉ ለሶስተኛ ወገን በማስተላለፍ እንዲተዳደር ለማከራየት
  • ሎት 4- ገዳመ እየሱስ ፓር ሙሉ ለሙሉ ለሶስተኛ ወገን በማስተላለፍ እንዲተዳደር ለማከራየት በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ በኪራይ ማስተላለፍ ይፈልጋል፡፡ በመሆኑም የተጠቀሱትን መስፈርት የሚያሟሉ ተጫራጮች ተጋብዘዋል፡፡
  1. ተጫራቾች በዘመኑ የታደሰ ህጋዊ የንግድ ፍቃድ ማቅረብ አለበት ፡፡
  2. ፓርኮቹ ውስጥ ገብቶ ለመስራት ፍቃደኛ የሆነና ከተቋማችን ጋር ውል ገብቶ በገበያ ጥናት እና የመነሻ ዋጋ መሰረት ተወዳድረው አስፈላጊውን ክፍያ የሚከፍልና በውሉ መሰረት ግዴታውን መወጣት የሚችል፡፡
  3. የሚሰጠውን አገልግሎት የሚገልጽ አጭር እና ግልጽ ፕሮፖዛል ማቅረብ አለበት፡፡
  4. በግቢ ያሉ ፋውንቴኖችንና መናፈሻዎችን የመጸዳጃ ቤቶችን የጽዳት የጥበቃ የተለያዩ ጥገናዎችን ከሌሎች ተከራዮች ጋር በመሆኑን ማስጠገን መቆጣጠርና በአግባቡ ማስተዳደር የሚችል፡፡
  5. ለህዝብ የሚሰጡ አገልግሎቶችን ተመጣጣኝ የገበያ ዋጋ ለማቅረብ ፍቃደኛ የሆነ፡፡
  6. ኮርፖሬሽኑና የከተማ አስተዳደሩ በሚያወጣው የስራ ሰዓት ቅዳሜ እና እሁድ በአላትን እንዲሁም ምሽትን ጨምሮ አገልግሎት መስጠት የሚችል፡፡
  7. አሸናፊነት ከታወቀ በኋላና ውል ከወሰደ በኋላ 3 ቀን ውስጥ ስራ መጀመር የሚችል፡፡
  8. ስታንዳርዱን የጠበቀ እና የኮሊደር ልማቱን የሚመጥን እቃዎችን ይዞ መግባት የሚችል፡፡
  9. ከተቻለ በሬስቶራንት በካፌ እና ህዝብ መዝናኛ ፓርክ ላይ ልምድ ያለውና መረጃ ማቅረብ የሚችል።
  10. ተጫራቾች ለሎት አንድ እና ሁለት 50,000.00 (ሃምሳ ብር) ሎት 3 እና 4 100,000.00 (አንድ መቶ ብር) የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ሲፒኦ ወይም ባን ጋራንቲ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የህዝብ መዝናኛ ቦታዎች አስተዳደር ኮርፖሬሽን ስም ከጨረታ ሰነድ ጋር ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
  11. ተጫራቾች የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ የማይመለስ 500 /አምስት መቶ ብር/ ቦሌ ማተሚያ ፊት ለፊት ገባ ብሎ የድሮው ፒኮክ መናፈሻ ግቢ ውስጥ ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ አስር ተከታታይ የስራ ቀን ከጠዋት 230 እስከ 1130 ሰዓት ድረስ በመቅረብ መግዛት ይቻላል፡፡
  12. ተጫራቾች የጨረታውን ሰነድ ፋይናንሻል መንት እና ቴክኒካል ዶክመንት ለየብቻ በማሸግ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ሳጥኑ እስከሚታሸግበት 10ኛው ተከታታይ የስራ ቀን በኋላ ባለው 11ኛው ቀን ጠዋት 400 ድረስ ለዚህ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው
  13. ጨረታው ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ 11ኛው የስራ ቀን ከጠዋቱ 400 ሰዓት ሳጥኑ ታሽጎ በዚያው ቀን ጠዋት 430 ቦሌ ማተሚያ ፊት ለፊት ገባ ብሎ የድሮው ፒኮክ መናፈሻ ግቢ በግዥና ንብረት ዳይሬክቶሬት ቢሮ ውስጥ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎች በተገኙበት ይከፈታል፡፡
  14. የጨረታ መክፈቻው ቀን ቅዳሜና እሁድ ላይ የሚውል ከሆነ በቀጣዩ ሰኞ በተጠቀሰው ሰዓት ተዘግቶ የሚከፈት ይሆናል፡፡
  15. ዘግይቶ የደረሰ የጨረታ ሰነድ ተቀባይነት የለውም፡፡
  16. ኮርፖሬሽኑ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው

ተጨማሪ መረጃ-ስልክ ቁጥር 0703614456 /0977246014 ደው መጠየቅ ይቻላል፡፡

 

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሕዝብ መዝናኛ ቦታዎች አስተዳደር ኮርፖሬሽን

 

Save Tender