Tender Detail

Tender Details

  • Company የደብረሲና የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል
  • Address ከአዲስ አበባ ወደ ደሴ በሚወስደው ዋና መንገድ ላይ 197 ኪሎ ሜትር ደብረሲና ከተማ ደ/ሲና : አማራ ክልል ፡ ኢትዮጵያ, Phone: 0913869679
  • Website
  • Deadline05 Jul 2025, 12:00 AM
  • magazine
  • Bid Document Price
  • opening date2025-07-05 00:00:00
  • Categories Transportation Service And Cargo

በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በጤና ጥበቃ ቢሮ የደብረሲና የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል በ2018 በጀት አመት ለሚፈፅማቸው ግዥዎች ማለትም ሎት 1. የሰራተኞች የትራንስፖርት ሰርቪስ አገልግሎት ግዥ፣ ሎት 2 የመድሃኒት ጭነት ከአዲስ አበባ እና ከደ/ብርሃን የኦከስጅን ስሊንደር ጭነት አገልግሎት ግዥ ለመፈፀም በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ከሀምሌ 1/2017 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ሰኔ 30/2018 ዓ.ም ለሶስተኛ ወገን በኮንትራት ለማሰራት ይፈልጋል፡፡


 

ግልፅ የጨረታ ማስታወቂያ

የጨረታ ቁጥር፡-01/2018

 

በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በጤና ጥበቃ ቢሮ የደብረሲና የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል 2018 በጀት አመት ለሚፈፅማቸው ግዥዎች ማለትም ሎት 1. የሰራተኞች የትራንስፖርት ሰርቪስ አገልግሎት ግዥ፣ ሎት 2 የመድሃኒት ጭነት ከአዲስ አበባ እና ከደ/ብርሃን የኦከስጅን ስሊንደር ጭነት አገልግሎት ግዥ ለመፈፀም በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ከሀምሌ 1/2017 . ጀምሮ እስከ ሰኔ 30/2018 . ለሶስተኛ ወገን በኮንትራት ለማሰራት ይፈልጋል፡፡

በዚህም መሰረት፡-

  1. በዘርፉ የታደሰ ንግድ ፈቃድ እና የንግድ ምዝገባ ሰርተፍኬት፣
  2. የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር /ቲን ነምበር/ ያላቸውና ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፤
  3. የሚሞሉት ጠቅላላ ዋጋ ከብር 200,000.00 /ሁለት መቶ ሺህ ብር/ እና በላይ ከሆነ የቫት ተመዝጋቢነት ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፣
  4. የጨረታ ሰነዱን ብር 150.00 /አንድ መቶ ሃምሳ ብር/ በመፈል ከሆስፒታሉ ግዥ ፋይ/ንብ/አስ//የስራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 62 መውሰድ ይችላሉ፡፡
  5. የጨረታ ማስከበሪያ ያስገቡትን ጠቅላላ ዋጋ 2% ያክሉን ለሆስፒታሉ CPO /በጥሬ ገንዘብ ማስያዝ አለባቸው
  6. ከብር 3.000.00 /ሶስት ሺህ ብር/ በላይ ለሚገዙ አገልግሎቶች 2% የመቁረጥ ግዴታ አለብዎት፡፡
  7. ለሰራተኞች ትራንስፖርት ጨረታ ተሽከርካሪው በወንበር (24) ሀያ አራት /ሰው/ እና በላይ የመጫን አቅም ያለው፡፡ እና የተሽከርካሪው የስሪት ዘመን እንደ ኤሮፓ አቆጣጠር 2010 እና ከዚህ ወዲህ የተመረተ፡፡
  8. ተጫራቾች የሚያስገቡት ዋጋ ለመኪናው የሚያስፈልጉ የተለያዩ ወጪዎችን እና የናፍጣ ፍያ በራሱ የሚፈን መሆኑን ታሳቢ አድርጎ ይሆናል፡፡
  9. ለሰራተኞች ትራንስፖርት ጨረታ ለሚሳተፉ የስራ ጊዜው በመንግስት የስራ ሰዓት መግቢያና መውጪያ ጠዋት፣ ምሳ ሰዓትና ማታ አገልግሎት መስጠት ሲሆን ለጭነት አገልግሎት ጨረታ ደግሞ ጭነት በሚኖርበት ጊዜ ብቻ ይሆናል፡፡
  10. ለሰራተኞች የትራንስፖርት እና ለጭነት አገልግሎት ጨረታ የተሸከርካሪው ሊብሬ በተጫራቹ ስም የሆነ፣ ኢንሹራንስ እና ሶስተኛ ወገን የተገባለት እንዲሁም የቴኒክ ምርመራ /ቦሎ/ ያሰራ መሆን አለበት፡፡
  11. ለሰራተኞች የትራንስፖርት ጨረታ ተሽከርካሪው በህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት የተመዘገበ እና ለጭነት አገልግሎት ደግሞ በደረቅ ጭነት አገልግሎት የተመዘገበ መሆን አለበት፡፡
  12. ለሁለቱም ሎቶች የሚያቀርበት ሰነድ ላይ ሙሉ አድራሻቸውን፣ ስማቸውን፣ ፊርማቸውን እና የድርጅታቸውን ማህተም ማስቀመጥ አለባቸው
  13. የሁቱም ጨረታዎች አሸናፊ ሆኖ የተመረጠው ድርጅት አሸናፊነቱ ከተገለፀለት 5 የስራ ቀናት በኋላ ባሉት 5 ቀናት ውስጥ ማስከበሪያ 10% ያሸነፉበትን ጠቅላላ ዋጋ CPO /በጥሬ ገንዘብ/ በማስያዝ ውል መውሰድ የሚችል መሆን ይኖርበታል የሁለቱም ለታዎች እንደ አስፈላጊነቱ በሩብ አመት፣ በግማሽ አመት ወይም የአንድ በጀት አመት የሚፈፀም ይሆናል፡፡
  14. ተጫራቾች የሚያቀርቡትን ነጣላ ዋጋና ጠቅላላ ዋጋ ዝርዝር አባሪ ዶክሜንቶችን ጨምሮ የጨረታ ሰነዱን ለዚሁ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ በፖስታ አሽገው ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
  15. ጨረታው ክፍት ሆኖ የሚቆየው የጨረታ ማስታወቂያው አየር ላይ ከዋለበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ 15 ቀናት ፍት ሆኖ ይቆይና 16ኛው ቀን ከጠዋቱ 300 ሰዓት የጨረታ ሳጥኑ ይታሸጋል፡፡
  16. ጨረታው 16ኛው ቀን ከጠዋቱ 330 ሰዓት ላይ በሆስፒታሉ የመሰብሰቢያ አዳራሽ ተጫራቾች ህጋዊ ወኪሎቻቸዉ በተገኙበት የሚከፈት ሲሆን ተጫራቾች ባይገኙም ጨረታዉ የሚከፈት ይሆናል
  17. ለሁለቱም ሎቶች ተጨማሪ መረጃዎችን ከጨረታው መመሪያና ከዋጋ መሙያ ላይ ማየት ይቻላል፡፡
  18. ጨረታው የሚከፈትበት ቀን የመንግስት የስራ ቀን ካልሆነ በቀጣይ ባለ የስራ ቀን ይከፈታል፡፡
  19. /ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
  20. ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 0913869679 0925402088 ወይም 0924854239 ደውለው ይጠይቁ፡፡

አድራሻ፡- ከአዲስ አበባ ወደ ደሴ በሚወስደው ዋና መንገድ 190 ሜትር ደብረሲና ከተማ

 

የደብረሲና የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል

 

Save Tender