በኢትዮጵያ ስኳር ኢንዱስትሪ ግሩፕ የኦሞ ኩራዝ ቁጥር-2 ሰኳር ፋብሪካ የተለያዩ ጥቅል 1 የጽሕፈት መሣሪያ ግዥ፤ ጥቅል-2-የጽዳት እቃ ግዥ እና ጥቅል 3 የአደጋ መከላከያ አልባሳት ግዥ እቃዎችን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
ብሔራዊ ግልፅ ጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር አግጨ/0013/ኦኩስፋ-2/2017
- በኢትዮጵያ ስኳር ኢንዱስትሪ ግሩፕ የኦሞ ኩራዝ ቁጥር-2 ሰኳር ፋብሪካ የተለያዩ ጥቅል 1 የጽሕፈት መሣሪያ ግዥ፤ ጥቅል-2-የጽዳት እቃ ግዥ እና ጥቅል 3 የአደጋ መከላከያ አልባሳት ግዥ እቃዎችን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
- በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልጉ ብቁ ተጫራቾች - የጨረታ ማስከበሪያ ሲፒኦ /CPO/ ወይም በቅድመ ሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የ90 ቀን የባንክ ዋስትና /BID BOND/ በመስኩ ህጋዊ የታደሰ የንግድ ሥራ ፍቃድ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር የተጨማሪ እሴት ታክስ ምዝገባ የምስክር ወረቀት ተጫራቾች በመንግስት ግዥ የዕቃና አገልግሎት አቅራቢዎች ዝርዝር /Supplier List/ ውስጥ መካተታቸውን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት እና በተጨማሪ የበጀት ዓመቱን ታክስ ክሊራንስ ምስክር ወረቀት ማቅረብ አለባቸው።
- ጨረታው በጋዜጣ ላይ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ 15 (አስራ አምስት) ቀን ውሎ በአስራ ስድስተኛው ቀን ይከፈታል። የጨረታውን መክፈቻ ትክክለኛ ቀን በጨረታ ሰነዱ ላይ በግልጽ ተቀምጧል። ዘግይቶ የሚቀርብ የመጫረቻ ሰነድ ውድቅ ይደረጋል።
- ብቁ ተጫራቾች በአማርኛ ቋንቋ የተዘጋጀውን የተሟላ የጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር 500.00 (አምስት መቶ ብር) በመክፈል ይህ ማስታውቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ ጨረታው መዝጊያ ቀን ድረስ ዘወትር በሥራ ሰዓት (ከሰኞ እስከ ዓርብ ከሰዓት በፊት ከ2፡00-6:00፣ ከሰዓት በኋላ ከ7:00- 10:30 እና ቅዳሜ ከሰዓት በፊት ከ2፡00-6፡00) ቀጥሎ በተመለከተው አድራሻ በመቅረብ መግዛት ይችላሉ።
- የጨረታው ሰነድ የሚሸጥበት ለውድድር የቀረበ ሰነድ የሚገባበትና የሚከፈትበት አድራሻ ቀጥሎ በተመለከተው ነው።
- በኢትዮጵያ ስኳር ኢንዱስተሪ ኦሞ ኩራዝ ቁጥር 2 ስኳር ፋብሪካ ማስተባበሪያ ቢሮ ቶታል ሶስት ቁጥር ማዞሪያ 300 ሜትር ከፍ ብሎ ተዘነኦ ሆስፒታል አጠገብ የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ህንጻ ግቢ ውስጥ ስልክ ቁጥር ፡- 0991149485 ወይም 0938309160
አዲስ አበባ/ ኢትዮጵያ
- ተጫራቾች ለሚወዳደሩባቸው ጥቅል ዕቃዎች ቀጥሎ የተመለከተውን የብር መጠን የጨረታ ማስከበሪያ በባንክ የተመሠከረለት የ90 ቀን ሲፒኦ (CPO) ወይም በቅድመ በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና BID BOND ከመጫረቻ ሰነዳቸው ጋር ለእያንዳንዱ ጥቅልሎች 10,000.00 (አስር ሺህ ብር ብቻ) ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል።
(ሎት 1) - የጽህፈት መሳሪያ ግዥ ሎት 2 የጽዳት እቃዎች ሎት-3 የአደጋ መከላከያ አልባሳት ግዥ
- የዕቃው ርክክብ የሚፈፀመው ኦሞ ኩራዝ ቁጥር-2 ስኳር ፋብሪካ አዲስ አበባ ማስተባበሪያ ቢሮ መጋዘን ነው።
- ጨረታው ጸንቶ የሚቆየው ጨረታ ከተከፈተበት ቀን ጀምሮ ለ60 ቀናት ነው።
- የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ጸንቶ የመቆያ ጊዜ የጨረታው ዋጋ ጸንቶ ከሚቆይበት የመጨረሻ ቀን በኋላ ለ28 ቀናት ነው።
- ፋብሪካ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ኦሞ ኩራዝ ቁጥር-2 ስኳር ፋብሪካ አዲስ አበባ ግዥ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት
Tel-0913369154/0940209464 Tel: 0991149485/0938309160
ሀይል ውሃ አዲስ አበባ
በኢትዮጵያ ስኳር ኢንዱስትሪ ግሩፕ የኦሞ ኩራዝ ቁጥር -2 ስኳር ፋብሪካ
