Tender Detail

Tender Details


የአ/አበባ ፖሊስ በ2017 በጀት ዓመት የተለያዩ ዕቃዎችን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።


 

የጨረታ ማስታወቂያ ቁጥር AAPC NCB 0010/2017 /

 

የአ/አበባ ፖሊስ 2017 በጀት ዓመት የተለያዩ ዕቃዎችን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት የሚፈልግ ሲሆን፡-

 

ሎት

የጨረታ ዓይነት

የናሙና መለያ

የጨረታ ማስከበሪያ ገንዘብ መጠን

 

001

የእስረኛ ቀለብ

በኮሚሸኑ ፍላጎት መሰረት

40,000

00

002

የአስክሬን መጠቅለያ ላስቲክ

በኮሚሽኑ ፍላጎት መሰረት ሆኖ የኮሚሽኑን ሳንፕል በማየት ናሙና የሚቀርብበት

40,000

00

003

Supply design installation commissioning and testing network access control (NAC) solution ግዥ

በኮሚሸኑ ስፔስፊኬሽን መሰረት

200,000

00

004

175-180 ሲሲ ጉልበት ያላቸው ሞተር ሳይክል

በኮሚሸኑ ስፔስፊኬሽን መሰረት

40,000

00

005

የታሸገ ውሃ ግዥ

በኮሚሽኑ ፍላጎት መሰረት ሆኖ 01 ዓመት የሚቆይ  በኮሚሽኑ ፍላጎት መሰረት

40,000

00

006

ለውሾች ቀለብ ሚሆን አጥንት የሌለው ስጋ

በኮሚሸኑ ስፔስፊኬሽን መሰረት

150,000

00

007

የተለያዩ መድሃኒቶች፣ የላብራቶሪ ሬኤጀንት እና የተለያዩ የህክምና መሳሪያዎች

በኮሚሸኑ ስፔስፊኬሽን መሰረት

100,000

00

008

በኤሌትሪክ የሚሰሩ ሞተር ሳይክሎች

በኮሚሸኑ ስፔስፊኬሽን መሰረት

100,000

00

009

ለሰነድ ምርመራና የሚሆን የቴክኖሎጂ ውጤቶች ግዥ ለሰነድ የሚረዳ መሳሪያ document forensic tools

በኮሚሸኑ ስፔስፊኬሽን መሰረት

300,000

00

010

የዘመናዊ በኬሚካል የሚሰራ ፎቶ ፕሪንተር

በኮሚሸኑ ስፔስፊኬሽን መሰረት

300,000

00

 

  1. በዘርፉ ህጋዊ ንግድ ፈቃድ ያላቸው መሆን እና በዘርፉ የተሰማሩ ለመሆናቸው በጀርባው ይመልከቱ የሚል ፅሁፍ በግልፅ ማቅረብ አለባቸው፡፡
  2. ተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ መሆን አለባቸው፡፡
  3. የታደሰ የዘመኑን ንግድ ፍቃድ እና የታደሠ ንግድ ምዝገባ ሰርተፍኬት ማቅረብ የሚችሉ መሆን አለባቸው
  4. የመንግስት /ቤቶች ለሚያወጡት ጨረታ ለመሳተፍ የሚያስችል የአቅራቢዎች የምዝገባ ሰርተፍኬት ማቅረብ አለባቸው፡፡
  5. በጨረታ ለመሳተፍ የሚያስችል ክሊራንስ ማቅረብ አለበት፡፡
  6. አማራጭ ዋጋ በዚህ ጨረታ ማቅረብ አይቻልም፡፡
  7. በጨረታ ለመሳተፍ የሚፈልጉ ሁሉ የጨረታ ውጤቱ እንደታወቀ ተመላሽ የሚሆን በሎቱ ፊት ለፊት የተቀመጠውን የገንዘብ መጠን የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ለአዲስ አበባ ፖሊስ ተብሎ በተዘጋጀው ከባንክ በተመሰከረለት .. ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
  8. ተጫራቾች ቴክኒካል ሰነዶችንና የዋጋ ማቅረቢያዎችን /ፋይናሻል/ ሰነዶች በተለያየ ፖስታ ታሽጎ ለየብቻ መቅረብ አለባቸው
  9. ማንኛውንም ተጫራቾች የሚያስገባው ሰነድ ፋይናሻል እና ቴክኒካል የጨረታ ሰነድ አንድ ኦሪጅናልና አንድ ኮፒ በተለያየ ፖስታ በማሸግ በፖስታው ላይ የጨረታ ሰነዱን ቁጥር የሚጫረትበትን ዕቃ አይነት በትክክል መፃፍ እንዲሁም በፖስታው ላይ ማህተም በመምታት ማስገባት ያለበት ሲሆን፣ ሰረዝ ድልዝ በፍሉድ የጠፋ ሰነድ ዋጋ ያልተሞላበት ዝርዝር ተቀባይነት የሌለው መሆኑን እናሳውቃለን፡፡
  10. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ የሚያሲዙት ... ከቴክኒክ ሰነዶችጋር በአንድ ላይ ታሽገው መቅረብ አለባቸው፡፡
  11. በጨረታ አሸናፊ የሆኑ ድርጅቶች ዕቃውን ወይም አገልግሎቱን በራሳቸው ትራንስፖርት /አበባ ከተማ ውስጥ በሚገኘው የኮሚሽኑ ዋና መስሪያ ቤት ግምጃ ቤት ወይም በከፍል 6 በፍላጎት መግለጫው በተጠቀሰው የማስረከቢያ ቦታ ድረስ በማምጣት ማስረከብ አለባቸው፣
  12. በጨረታ ሰነድ በክፍል 6 ውስጥ በሚገኘው የፍላጎት መግለጫ ላይ በሚገለፀው መሰረት ጨረታ ሰነዱ ላይ በቀረበው መሰረት ናሙና ማቅረብ አለበት፡፡
  13. ተጫራቾች ያቀረቡት ናሙናም ሆነ አሸናፊ መሆናቸው ሲረጋገጥ ያቀርቡአቸው ዕቃዎች ኮሚሽኑ ባወጣው ፍላጎት መግለጫ /specification/መሰረት መሆኑን በኮሚሽኑ የጥራት ኮሚቴ ወይም በኢትዮጵያ ተስማሚነት ምዘና ኤጀንሲ አማካኝነት የሚረጋገጥ ይሆናል
  14. ተጫራቾች አራዳ ጊዮርጊስ /ክርስቲያን ከፍ ብሎ በሚገኘው የኮሚሽኑ ዋና መስሪያ ቤት 5 ፎቅ ግዢ /ቤት ቢሮ ቀርበው በእያንዳንዱ የጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር 200.00 /ሁለት መቶ ብር/ በመክፈል መግዛት ይችላሉ፣
  15. ተጫራቾች ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን አንስቶ ባሉት 15 የስራ ተከታታይ ቀናት ውስጥ ከጠዋቱ 230 እስከ 1130 ሰዓት ድረስ እንዲሁም በማግስቱ 16ኛው ቀን እስከ ጠዋት 430 ሠዓት ድረስ ጨረታው ክፍት ሆኖ ስለሚቆይ በኮሚሽኑ ግዢና ፋይናንስ 5 ፎቅ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይችላሉ
  16. በጨረታ ሰነዱ ክፍል 2 ላይ በሚጠቀሰው ቀን ከጠዋቱ 430 ሰዓት የጨረታ ሳጥኑ ታሽጎ 500 ሰዓት ሲሆን በመ/ቤቱ 5 ፎቅ ትንሹ አዳራሽ ቢሮ ቁጥር 512 ይከፈታል፣
  17. የጨረታው ፈቻ የስራ ቀን ካልሆነ ቀጥሎ ባለው መደበኛ የስራ ቀን ከላይ በተጠቀሰው 430 ሰዓት ታሽጎ 500 ሲሆን ይከፈታል፡፡
  18. ዘግይተው የሚመጡ የጨረታ ሰነዶች ተቀባይነት የላቸውም፡፡
  19. መስሪያ ቤቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ በከፊልም ሆነ በሙሉ ጨረታውን የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡

ለበለጠ መረጃ በስ/ቁጥ 011 862 5800 (011 111 0448)

 

የአ/አበባ ፖሊስ

 

 

Save Tender