Tender Detail

Tender Details

  • Company Ethiopian Engineering Corporation (የኢትዮጵያ ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን)
  • Address ከመገናኛ አደባባይ ወደ ኢትዮጵያ አየር መንገድ በሚወስደው ዋና ቀለበት መንገድ ወደ አደይ አበባ ስታዲዬም (የኢትዮጵያ ወጣቶችና ስፖርት ማእከል) የሚያስገባው መገንጠያ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የሚሰጥበት ህንጻ ቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 05 : አዲስ አበባ ፡ ኢትዮጵያ, Phone: +251 118720722
  • Websitehttps://eec.com.et/
  • Deadline09 Jul 2025, 12:00 AM
  • magazineAddis Zemen
  • Bid Document Price
  • opening date2025-07-09 00:00:00
  • Categories General Service Provision , Business, Industry And Factory Foreclosure

የኢትዮጵያ ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን ከዚህ በተጨማሪ በጂኦቴክኒካልና ጂኦሎጂካል ሥራዎች፣ በቅየሳ፣ በላቦራቶሪ ምርመራና ሥልጠና መስክ አገልግሎቶችን እየሰጠ ሲሆን፤ ኮርፖሬሽኑ የተቋቋመበትን ዓላማ ከግብ ለማድረስ በግብዓትነት የሚያስፈልጉ ጥራታቸውን የጠበቁ ቋሚና አላቂ ዕቃዎችን በቅድመ ብቃት ማረጋገጫ ማጣሪያ ግልጽ ጨረታ መሰረት በመለየት በአቅራቢነት በመመዝገብ በወቅቱና በጥራት አገልግሎቶችን ሊያቀርቡ የሚችሉትንና በቀጣይና በዘላቂነት ከኮርፖሬሽኑ ጋር አብሮ ለመስራት ፈቃደኛ የሆኑ ድርጅቶችን በመለየትና በማወዳደር ለቀጣይ ውድድር መጋበዝ ይፈልጋል፡፡


 

ግልፅ የጨረታ ማስታወቂያ

የቅድሚያ ብቃት ማረጋገጫ ማጣሪያ ግልጽ ጨረታ ቁጥር /ቅብማማ02/2017

 

የኢትዮጵያ ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን የሀገሪቷ ቁልፍ የመሰረተ ልማት ፍላጎቶች በሆኑት በመንገድና ድልድይ፣ በውኃና ኢነርጂ፣ በህንጻና ከተማ ልማት እንዲሁም በሌሎች የሲቪል ምህንድስና ሥራዎች በሚፈለገው ጊዜ፣ መጠንና ጥራት በማቅረብ በኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪው ዘርፍ በዲዛይንና በግንባታ ሥራዎች መስክ አገልግሎት በመስጠት ላይ የሚገኝ የመንግስት የልማት ድርጅት ነው። ከዚህ በተጨማሪ በጂኦቴክኒካልና ጂኦሎጂካል ሥራዎች፣ በቅየሳ፣ በላቦራቶሪ ምርመራና ሥልጠና መስክ አገልግሎቶችን እየሰጠ ሲሆን፤ ኮርፖሬሽኑ የተቋቋመበትን ዓላማ ከግብ ለማድረስ በግብዓትነት የሚያስፈልጉ ጥራታቸውን የጠበቁ ቋሚና አላቂ ዕቃዎችን በቅድመ ብቃት ማረጋገጫ ማጣሪያ ግልጽ ጨረታ መሰረት በመለየት በአቅራቢነት በመመዝገብ በወቅቱና በጥራት አገልግሎቶችን ሊያቀርቡ የሚችሉትንና በቀጣይና በዘላቂነት ከኮርፖሬሽኑ ጋር አብሮ ለመስራት ፈቃደኛ የሆኑ ድርጅቶችን በመለየትና በማወዳደር ለቀጣይ ውድድር መጋበዝ ይፈልጋል፡፡

በመሆኑም፡-

  1. ተመዝጋቢዎች አግባብነት ያለው የታደሰ የንግድ ፈቃድ፣ የዘመኑን ግብር የከፈሉ፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ ከፋይነት የተመዘገቡ መሆናቸውን የሚያሳይ የምስክር ወረቀት የሚያቀርቡ፣ ግብር የመክፈል ግዴታቸውን የተወጡ መሆኑን የሚያረጋግጥ እንደዚሁም በአቅራቢዎች ዝርዝር ውስጥ የተካተቱ እና መመዝገባቸውን የሚያሳይ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፣
  2. ተመዝጋቢዎች የድርጅታቸውን አሁናዊ ገፅታ የሚያሳይ ፐሮፋይል፣ የሥራ አፈጻጸምን የሚገልፅ ማስረጃ፣ በኦዲት የተረጋገጠ የትርፍ እና ኪሳራ የሂሳብ መግለጫ የቅርብ ዓመት፣ ከጥራት (ISO Certificate) እና ብቃት ጋር የተያያዙ ሌሎች መረጃዎቸ ማስያዝ ይችላሉ፡
  3. ተወዳዳሪዎች የሚመዘገቡባቸው የውድድር ዘርፍ
  4. ተወዳዳሪዎች በጨረታ ሰነዶቻቸው ላይ ስማቸውን ሙሉ አድራሻቸውን፣ ፊርማቸውን እና የድርጅታቸውን ማህተም ማስፈር አለባቸው።
  5. ተመዝጋቢዎች ጨረታው በጋዜጣ ላይ ከወጣበት ዕለት አንስቶ ለተከታታይ 10 (አስር) ቀናት ክፍት ሆኖ ስለሚቆይ ዘወትር በሥራ ሰዓት ኮርፖሬሽኑ ያዘጋጀውን ፎርም (ቅጽ) በመውሰድ አስፈላጊውን የድርጅታችሁን መረጃዎች በመሙላት፣ ፊርማና ማኅተም በማድረግ ከታች በተጠቀሰው አድራሻ ሰነዳቸውን በተዘጋጀው ሳጥን ማስገባት ይችላሉ።

አድራሻ፡- የኢትዮጵያ ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን

ሕንጻ 1 4 ፎቅ፣ በኮርፖሬት አገልግሎቶች ቢሮ፣ ኮርፖሬት ገዥ ቡድን

ቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 05

ስልክ ቁጥር - +251 11 872 0722

ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን

ኢትዮጵያ አዲስ አበባ

 

የኢትዮጵያ ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን

 

Save Tender