የክርስቲያን በጎ አድራጎትና የልማት ማህበራት ህብረት CCRDA በራሱ ህንፃ ውስጥ የሚገኘውን ካፍቴርያና ኪችን ከእቃው ጋር ለማከራየት ይፈልጋል::
Consortium of Christian Relief and Development Association (CCRDA)
በድጋሜ የወጣ የካፍቴሪያ ኪራይ/አገልግሎት የጨረታ ማስታወቂያ
የክርስቲያን በጎ አድራጎትና ልማት ማህበራት ህብረት CCRDA ከ500 በላይ አባላት ያሉትና ከ50 ዓመታት በላይ በልማትና በጎ አድራጎት ሥራ ላይ በማገልገል ላይ የሚገኝ ድርጅት ነው::
ድርጅቱ በራሱ ህንፃ ውስጥ የሚገኘውን ካፍቴርያና ኪችን ከእቃው ጋር ለማከራየት ይፈልጋል:: ስለዚህ መከራየት የሚፈልጉ ተጫራቾች ለድርጅቱ የተለያዩ ዝግጅቶች አገልግሎት ለመስጠት የሚችሉ በሞያው ልምድ ያላቸው መሆን አለባቸው:: ተጫራቾች በድርጅቱ ቅጥር ጊቢ የሚገኘውን ካፍቴሪያና ኪችን በአካል ቀርበው ከተመለከቱ በኋላ ቀጥሎ የተዘረዘሩትን በማሟላት መጫረት ይችላሉ፡፡
- ለተለያዩ የባህልና የውጪ ምግብ ዓይነቶች በመደበኛ ግብአቶች (Recipe) እና መጠን (Standard Portion) የምግብ ዝርዝር (Menu) ዋጋ ማቅረብ
- ከዚህ ቀደም በሞያው ያላቸውን የሥራ ልምድ የሚያሳይ ማስረጃ
- የግብር ከፋይ (Tin No) ቅጂ
- የቫት ተመዝጋቢ የምስክር ወረቀት ቅጂ
- የታደሰ የንግድ ፈቃድ ቅጂ ማቅረብ አለባቸው
- ተጫራቾች የጨረታ ዋስና ብር 20,000.00 (ሃያ ሺህ ብር) በሲፒኦ ማስያዝ ይኖርባቸዋል
ተጫራቾች ለመከራየት የሚያቀርቡትን ዋጋ ከላይ በዝርዝር ከተጠቀሱት ማስረጃዎች ጋር በማያያዝ በክርስቲያን በጎ አድራጎትና ልማት ማህበራት ህብረት መ/ቤት ለዚሁ ጉዳይ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ይህ ማሰታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ7 ተከታታይ ቀናት ውስጥ ቢሮ ቁጥር 304 ማስገባት ይኖርባቸዋል።
የክርስቲያን በጎ አድራጎትና የልማት ማህበራት ህብረት የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ቢሮ ቁጥር 103 ማግኘት ይችላሉ፡፡
የክርስቲያን በጎ አድራጎትና የልማት ማህበራት ህብረት
አድራሻ፡- ቃሊቲ ከአሽከርካሪዎችና ሜካኒኮች ማሰልጠኛ ማዕከል ፊት ለፊት
ስልክ 0114-390322 ወይም 0114-393393
