የኦሮሚያ ግብርና ህብረት ስራ ማህበራት ፌዴሬሽን ኃ/የተወሰነ የአሰላ ብቅል ፋብሪካ የተለያዩ ያገለገሉ ተሽከርካሪዎችን እና ቋሚ ዕቃዎችን ባሉበት ሁኔታ በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል።
የኦሮሚያ ግብርና ህብረት ሥራ ማህበራት ፌዴሬሽን ኃ/የተ. አሰላ ብቅል ፋብሪካ
የተለያዩ ያገለገሉ ተሽከርካሪዎች እና ቋሚ ዕቃዎች ሽያጭ የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር OACE, AMF/MS/02/2017
የኦሮሚያ ግብርና ህብረት ስራ ማህበራት ፌዴሬሽን ኃ/የተወሰነ የአሰላ ብቅል ፋብሪካ የተለያዩ ያገለገሉ ተሽከርካሪዎችን እና ቋሚ ዕቃዎችን ባሉበት ሁኔታ በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል።
ስለሆነም በጨረታው ለመወዳደር ፍላጎትና አቅም ያላቸው ተጫራቾች ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች ማሟላት አለባቸው።
- ተጫራቾች የ2017 ዓ.ም የታደሰ የንግድ ፍቃድ፣ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር /TIN No/ ተመዝጋቢስለመሆናቸው ሕጋዊ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ መሆን ይኖርባቸዋል።
- በዘርፉ ህጋዊ የሆነ የንግድ ፈቃድ ያላቸው።
- የጨረታ ሰነዱን ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ የማይመለስ ብር 500.00 (አምስት መቶ) በፋብሪካችን አካውንት በኢትዮጰያ ንግድ ባንክ 1000257808697 ወይም በኦሮሚያ ህብረት ስራ ባንክ 1000043405229 ገቢ በማድረግ ዘወትር በስራ ሰዓት ከሰኞ እስከ ዓርብ ጠዋት 2፡00-6፡00 ከሰዓት በኋላ ከ7፡00-10፡00 ሰዓት ቅዳሜ ጠዋት 2፡00- 6:00 ሰዓት ድረስ አሰላ-ቁሉምሳ በሚገኘው ፋብሪካችን ቢሮ ቁጥር 051 ወይንም አዲስ አበባ በሚገኘው ዋና መ/ቤት ከጀርመን አደባባይ ወደ ሚካኤል አደባባይ በሚወስደው መንገድ ላይ ሚካኤል ቤ/ክርስቲያን አጠገብ በሚገኘው የኦሮሚያ ግብርና ህብረት ስራ ማህበራት ፌዴሬሽን ህንፃ ቢሮ ቁጥር 6 ሰነዱን መግዛት ይችላሉ።
- ተጫራቾች የሚጫረቱበትን ተሽከርካሪዎች /ቋሚ ዕቃዎች ጠቅላላ ዋጋ 5% የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና በባንክ በተመሰከረለት ሲ.ፒ.ኦ /C.PO/ ማስያዝ ይኖርባቸዋል።
- ይህ የጨረታ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ ሐምሌ 25 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ድረስ በአየር ላይ ክፍት ሆኖ ይቆያል።
- ተጫራቾች በኤንቨሎፕ የታሸገ የጨረታ ሰነዳቸውን በአሰላ ብቅል ፋብሪካ ቢሮ ቁጥር 051 በተቀመጠው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው።
- ጨረታው በዕለቱ ሐምሌ 25 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ በ8፡00 ሰዓት ተዘግቶ በዕለቱ በ8፡15 ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት አሰላ ቁሉምሳ/ በሚገኘው የፋብሪካችን የመሰብሰቢያ አዳራሽ ይከፈታል።
- ተሽከርካሪዎቹን ከላይ በተራ ቁጥር 3 በተለገጹት የስራ ቀናት አሰላ/ቁሉምሳ በሚገኘው የፋብሪካው ግቢማንነታቸውን የሚገልጽ መታወቂያ በመያዝ በአካል በመገኘት ማየት ይችላሉ።
- የጨረታ ሳጥኑ ከታሸገ በኋላ የጨረታ ሰነዳቸውን የሚያቀርቡ ተጫራቾች ተቀባይነት አይኖራቸውም።
- ፋብሪካው የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለተጨማሪ ማብራሪያ፡-
ስልክ ቁጥር፡- 022 331 52 66 ወይም 022 331 81 97 ደውሎ መጠየቅ ይቻላል።
የኦሮሚያ ግብርና ህብረት ሥራ ማህበራት ፌዴሬሽን ኃ/የተ. አሰላ ብቅል ፋብሪካ
